Hiwote

Hiwote

Share

like the page and share information with me ሁሉም ሰዉ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት::

26/05/2024

🔯🌀 ትልቅ መልዕክት🌀🔯

✅ፍቅር የለም ከማለትህ በፊት፣ እኔ ውስጥ ፍቅር አለ ወይ? ብለህ ፈትሽ!

✅ሚስት የምትሆን ሴት የለችም ፣ ከማለትህ በፊት እኔ ባል መሆን ችላለሁ ወይ? ብለህ ራስህን መርምር!

✅ወንድ እንጂ ባል የለም ከማለትሽ በፊት፣ እኔ ጥሩ ሚስት መሆን ችላለሁ ወይ? ብለሽ ራስሽን ጠይቂ!

✅ጥሩ ጉዋደኛ የለም ከማለትሽ በፊት እኔ ጥሩ ጉዋደኛ መሆን ችላለሁ ወይ? ብለሽ አስቢ!

✅ማንም ሰው ጥሩ ከሆነ፣ ጥሩ ነገሮች ሁሉ ከሱ መራቅ አይችሉም።

ስለዚህ ጥሩነትን ከሰው ሳይሆን ከራሳችን ነው የምናገኘው።
መልካም ሁን፣
ቅን ሁን፣
ትሁት ሁን፣
ወዳጅ ሁን፣
ፍቅር ሁን፣
ሩህሩህ ሁን፣
ለጋሽ ሁን፣
አስተዋይ ሁን፣
ደስተኛ ሁን፣
ሳቂተኛ ሁን፣
መፍትሄ ሰጪ ሁን፣
ተፅዕኖ ፈጣሪ ሁን፣
አመስጋኝ ሁን፣
በትንሽ የምትደሰት ሁን፣
ብልህ ሁን፣
አስታዋሽ ሁን፣......ወዘተ......
በምድር ላይ ከሰው ልጆች ውጪ ምንም ውድ ነገር
የለም። አንተን የሚገዛ የገንዘብ መጠን የለም።
ለራስህ ክብር ስጥ
አንተ ውድ መሆንህን ካመንህ ሰዎችም ውድ መሆናቸውን አትዘንጋ
አክብራቸው ሰው በመሆናቸው ብቻ!!!

ሼርርርር

25/05/2024

🌀🌀 "ሀሉም በጊዜው ይሆናል"! 🌀🌀

✅ ያለ ሰዓቱ አይነጋም!"

✅ ጨርሶ አይጨልምም።

👉 ፀሐይ ስትጠልቅ፣ ጨረቃና ከዋክብት ይወጣሉ።

👉 ዘጠኝ በሮች ሲዘጉ አንዱ ይከፈታል።

👉 ዘጠኝ ወዳጆች ሲሄዱ አንዱ ይተርፋል።

👉 ፀሐይ ባትጠልቅ ጨረቃ አትታይም። ፈተና ካልመጣምየማናውቃቸው ሰዎች አሉ።

👉 ፈተናው የሚሰጠን የመጨረሻ ውጤት የቅርብ ያልነው ሩቅ፣ የሩቅ ያልነው የቅርብ መሆኑን ነው።

👉 ፀሐይ እንደምትወጣ እርግጠኞች ነን።
👉 ጨረቃና ከዋክብት ለመውጣታቸው ግን እርግጠኛ አይደለንም።

👉 ጨረቃ የማትወለድበት፣ ከዋክብት የሚሰወሩበት ጊዜ አለ።

👉 የምታስተማምነዋ ፀሐይ ስትጠልቅ ያልጠበቅናቸው ጨረቃና ከዋክብት ይወጣሉ።

👉 የማታ ብርሃኖች ዙሪያውን በደንብ ባያሳዩንም ለእግራችን መርገጫ ያሳዩናል።

👉 ሰማዩን በውበት ይገልጡልናል። የብርሃንን ዋጋ እንድናስብና እንድንሰስት ያደርጉናል።

👉 እንደ ፀሐይ እርግጠኛ የሆንባቸው ሊጠልቁ ይችላሉ።

👉 ያልጠበቅናቸው ደግሞ ብቅ ይላሉ። ጨርሶ አይጨልምምና።

👉 “ፀሐይ ስለ መጥለቋ ከተመረርህ ከዋክብትም ይሰወሩብሃል” ይባላል።

👉 ቢወጡም አታያቸውም ማለት ነው።

👉 ምሬት ዓይንን ያጨልማልና።

🌀✅ #አዎ ያለ ሰዓቱ አይነጋም።

👉 አሁን ለመተኛት ገብተን ወዲያው ቢነጋ መልካም አይደለም።

🌀✅ #ያለ ሰዓቱ ከነጋ፡-

1️⃣ "አእምሮአችን አይታደስም፡-

👉 አእምሮ የሚታደሰው የዋልንበትን አሳብ ፍጹም ትተን ስናርፍ ነው።

👉 በቂ ዕረፍት ስናገኝ ለቀጣዩ ቀን መማርና መሥራት እንችላለን።

👉 በሕይወት ውስጥ የሚገጥመን የፈተና ሰዓትም ራሳችንንና ዙሪያችንን እንድናይ ስለሚረዱን ያበስሉናል።

🌀✅ እኔ ማን ነኝ?

👉 የምኖረው ከእነማን ጋር ነው? የሚለውን ጥያቄ መመለስ የምንችለው በመከራ ሰዓት ነው።

👉 የፈተና ቀኖች የጠለለ አሳብን፣ የተጣራ ወዳጅን ያስቀሩልናል።

👉 ለቀጣዩ ዘመንም በቀላሉ የማይበገር አእምሮን ያጎናጽፉናል።

👉 ያለ ሰዓቱ ካልነጋ አንበስልም።

👉 እኛ የሚያስጨንቀን መከራው ነው፣ ጌታ ግን ትምህርቱ እንዳያልፈን ያስባል።

👉 ሕጻን ልጅ ስለ መድኃኒቱ ምሬት ያለቅሳል፣ ወላጆች ግን ስለመዳኑ ይጨክናሉ።

👉 ሩኅሩኁ ጌታ እስክንማር ይጨክናል።

2️⃣ "ከድካም አንላቀቅም፡-

👉 ያለ ሰዓቱ ከነጋ አሁን የተለየነው ግርግር መልሶ ይመጣል።

👉 አሁን የተውነውን ሥራ እንቀጥላለን።

👉 ከድካም ስለማንበረታ በቀጣዩ ቀን እንደክማለን፣ እንወድቃለን፣ በሥራችንም ውጤታማ አንሆንም።

👉 የቀጣዩን ቀን ትግል ለመቋቋም በሰዓቱ መንጋት አለበት።

👉 እግዚአብሔር ከግርግሩ ለይቶ፣ ሱስ ከሆኑብን የጊዜ ገዳዮች አውጥቶ የሚያሳርፈን በጨለማ ቀኖች ነው።

👉 በሰዓቱ ሲነጋ በርትተን ለቀጣዩ ዘመን ኃይል ይዘን እንቆማለን።

👉 በሰዓቱ ይንጋ፣ በትግሎቻችን ሁሉ ጌታ ትዕግሥት ይስጠን።

✅ የማይነጋ ሌሊት የለም።
✅ ማታ ጠዋት ይሆናል።
✅ ማታ የተለየን ጠዋት ይመጣል።

🌀👉 ጠዋት ሲመጣ ግን በሰዓቱ ነግቷልና አእምሮአችን ታድሶ፣ አቅማችን በርትቶ እንቀበለዋለን።

#ፈጣሪ ጸጋውን ያብዛልን!
#ሀገራችንና ህዝቦቿን ከክፉው ሁሉ ይጠብቅልን!"(አሜን)
ሼርርርር

Want your public figure to be the top-listed Public Figure in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Address

Addis Ababa