Addis Ababa Times

Addis Ababa Times

Share

እንኳን ደህና መጡ !
ለዜና ፣ወቅታዊ ጉዳዮች፣መዝናኛ ፍላጎት?

Photos from Addis Ababa Times's post 07/10/2025

" ' የመኪናና የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ተሰርቆብኛል ' የሚል አካል ልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመምጣት ዕቃውን መለየትና መረከብ ይችላል " - ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በአዲስ አበባ አስራ አንዱም ክ/ከተማ ተከታታይነት ያለው በወንጀለኞችና የተሠረቁ ዕቃዎችን በሚቀበሉ ግለሠቦች ላይ የጥናት፣ የክትትል፣ የምርመራና የኦፕሬሽን ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጿል።

ከነሐሴ 22 እስከ 24 ቀን 2017 ዓ/ም በልደታ ክ/ከተማ ሦስት ወረዳዎች፤ በወረዳ 3፣ 7 እና 9 የተሠረቁ የመኪና ዕቃዎችንና የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን እየገዙ የሚሸጡ ግለሠቦችን እንደለየ አመልክቷል።

ልዩ ቦታው ፦
- ጌጃ ሰፈር፣
- ሱማሌ ተራ
- አብነት አካባቢዎች በተለያዩ መኖሪያ ቤቶችና ሱቆች ላይ የፍርድ ቤት የመበርበሪያና የመያዣ ትዕዛዝ በማውጣት በተደረገ ብርበራ የተለያዩ የመኪናና የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ከሌባ የሚገዙና የሚቀበሉ ግለሰቦችን ይዟል።

ፖሊስ አደረኩት ባለእ ኦፕሬሽን ፦
➡️ 209 የጎን መስታወት (ስፖኪዮ)፣
➡️ 84 ፍሬቻ፣
➡️ 6 የፊት መብራት፣
➡️ 56 ጌጅ፣
➡️ 32 የመኪና ጌጥ፣
➡️ 66 ቸርኬ፣
➡️ 11 የተሽከርካሪ ዓርማ፣
➡️ 7 የኤሌክትሪክ ቻርጀሮች፣
➡️ 34 የመኪና ሠሌዳዎች፣
➡️ 13 ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣
➡️ 4 ዴስክቶፕ ኮምፒውተር፣
➡️ 41 የሞባይል ቀፎዎች እንዲሁም የተለያዩ ሀሠተኛ ሠነዶችን ከ4 ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ እንደሆነ አመልክቷል።

የመኪናና የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ተሰርቆብኛል የሚል አካል ልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመምጣት ዕቃውን መለየትና መረከብ እንደሚችልም ፖሊስ አስታውቋል፡፡



አዲስ አበባ

Want your public figure to be the top-listed Public Figure in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address

Ethiopia, Arada Sub City
Addis Ababa