Awulala Multimedia
ነፃ ሀሳብ ፤ ሚዛናዊ መረጃ። Awulala Multimedia is Ethiopia's premier real estate multimedia platform.
21/11/2019
የኢህአዴግ ምክር ቤት የፖርቲውን ውህደት አፀደቀ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ምክር ቤት የድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የመራለትን የፖርቲውን ውህደት አፀደቀ።
የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ምክር ቤት በዛሬው እለት ማካሄድ በጀመረው ስብሰባ ነው ውህደቱን ያፀደቀው።
የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በቅርቡ ባካሄደው ስብሰባ በውህድ ፓርቲ ፕሮግራም (ማኒፌስቶ) ላይ ዝርዝር ውይይት እና ክርክር በማካሄድ ረቂቁ ለኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲቀርብ መወሰኑ የሚታወስ ነው።
በተመሳሳይ ስራ አስፈፃሚው በተዋሃደው ፓርቲ ሕገ ደንብ ላይ ተወያይቶ እንዲጸድቅ ለኢህአዴግ ምክር ቤት እንዲመራ መወሰኑ ይታወሳል።
የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ አባል አቶ ፍቃዱ ተሰማ በዛሬው እለት የምክር ቤቱን ስብሰባ አስመልክተው ለኢቢሲ እንደተናገሩት፥ ምክር ቤቱ ባካሄደው ስብሰባው በፖርቲው ውህደት ዙሪያ ተወያይቱ ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቀዋል።
በዚህም ምክር ቤቱ በኢህአዴግ ውህደትን በሙሉ ድምጽ ማጽደቁን ነው አቶ ፍቃዱ የተናገሩት።
(ዘገባ የፋና)
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Website
Address
Addis Ababa