Fidel Tube
Welcome to my Channel
ፊደል Tube
04/05/2020
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 5 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 1,758 ላቦራቶሪ ምርመራ 5 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 140 ደርሷል።
25/04/2020
እስክንድር ነጋ በአሁን ሰዓት ኮልፌ ፖሊስ መምሪያ እንደሚገኝ ፓርቲው አስታውቋል
የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲፕሬዝዳንት አቶ እስክንድር ነጋ ዛሬ ሚያዚያ 17/2012 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ ከቤታቸው እንደወጡ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኮማንድ ፖስት የእስር ትዕዛዝ መታሰራቸውን በፌስቡክ ገጹ ያስታወቀው የፓርቲው ቃል አቀባይ አቶ ስንታየሁ ቸኮል “በአሁን ሰዓት ኮልፌ ፖሊስ መምሪያ እንዳለ አረጋግጠናል” ሲል በድጋሚ አስታውቋል፡፡
አቶ እስክንድር “…ኮልፌ ቀራኒዮ ወረዳ 05 የድሆችን ቤት ፈረሳን አስመልክቶ ለምን ተገኘህ…” በሚል እንዳሰራቸውም ነው ቃል አቀባዩ በገጻቸው ያሰፈሩት፡፡
20/04/2020
ልዩ የስራ ጠባይ ላላቸውና ድጋፍ ለሚሹ የይለፍ ፍቃድ እየተሰጠ ነው
ከኮድ-2 ተሽከርካሪዎች የፈረቃ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ልዩ የስራ ጠባይ ላላቸውና ልዩ ድጋፍ ለሚሹ የተሽከርካሪ የይለፍ ፍቃድ እየሰጠ መሆኑን የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡
ከዛሬ ጀምሮ እንዲተገበር ሆኖ ከወጣው የፈረቃ እንቅስቃሴ መመሪያ ጋር በተያያዘ ጥያቄ ያላቸው አካላት ወደ ባለስልጣኑ እየመጡ ነው ያሉት የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ይግዛው ዳኘው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተቀመጠው የልዩ ድጋፍ አሰጣጥ መመሪያ መሰረት እየተስተናገዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ለጤና እና ፋርማሲ ባለሙያዎች፣ ለሚዲያ አካላት እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች አዋጁን ለማስፈጸም በወጣው የትራንስፖርት ስምሪት መመሪያ አንቀጽ 10 ንዑስ አንቀጽ 3 መሰረት በተቋቋመው የቴክኒክ ኮሚቴ እየታየ የይለፍ ወረቀት እየተሰጣቸው እንደሆነም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ:አላይን አማሀሪክ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Website
Address
Opening Hours
| 00:00 - 12:00 |