Tourism Training Institute

Tourism Training Institute

Share

It is established as an autonomous legal executive entity of the Federal Government Ethiopia. The institute shall have the following
objectives:
1.

Photos from Tourism Training Institute's post 21/05/2026

በመረጃ አያያዝ የደረሰበትን ደረጃ የሚያሳይ ''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በሚል የተዘጋጀ ኤግዚቢሽን ተጎበኘ።
ቱ ማ ኢ
ግንቦት /2018 ዓ ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ሰራተኞች ‎ ''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉዓላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችውን ትልቅ ድል የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ጎብኝተዋል።

‎መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ ነው።
መረጃ የተዋሰ ወይም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ ሀገራዊ አጃንዳን ለማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ተብሏል።
በኤግዚብሺኑ ‎ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች እውቀትና ክህሎት መሰራቱ ለየት ያደርገዋል ።
ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን እንዳለበት በባለሙያዎቹ ተገልጿል።
ኤግዚቢሽኑን ያዘጋጁት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ኤጄንሲ እና የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ናቸው።

ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/

Travel Ethiopia-ጉዞ ኢትዮጵያ 04/05/2026

https://youtu.be/Vxf0X4wyru4?si=CZjZorpneOat9X0g

Travel Ethiopia-ጉዞ ኢትዮጵያ 31 likes, 1 comment. "ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ጀርባ-የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት "

Photos from Hawassa University's post 04/05/2026
Photos from Tourism Training Institute's post 03/05/2026

በቱሪዝም ዘርፍ ያሉ አቅሞችን አሟጦ ለመጠቀም ተቋማት ተቀናጅተው መሥራት ይጠበቅባቸዋል ተባለ።
ቱ.ማ.ኢ
ሚያዚያ 25/218 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከሀዋሳ ዩንቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ጉባኤ ማጠቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የዩንቨርሲቲው ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ በዘርፉ የሚገባውን ጥቅም ለማግኘት በቴክኖሎጂ እና በፈጠራ ታግዘው ሁለቱ ተቋማት ቢሰሩ እንደሀገር በዘርፉ ለውጥ ማምጣት እንችላለን ብለዋል።

በጥናትና ምርምር ጉባኤው ከቀረቡ የጥናት ወረቀቶች አንዱ በሲዳማ ክልል ያለውን የምግብ ቱሪዝም ሀብት የሚያሳይ ሲሆን በሚገባ ማስተዋወቅና ክልሉም ተጠቃሚ እንዲሆን መስራት እንደሚገባ የሚዳስስ ነው።
አጥኚው የኢንስቲትዩቱ አሰልጣኝ ጌትሽ ገደፋው ሲሆኑ በገለፃቸው በዓለም ላይ በምግብ ቱሪዝም የሚታወቁ ከተሞችን እንደምሳሌ አቅርበዋል።
ሌላው የጥናት ጽሑፍ አቅራቢ ከወልዲያ ዩንቨርስቲ አቶ ጌታቸው ከበደ 'Reimagining Tourism as Catalysts for Ethiopia 's Multi_Sectoral Transformation in the Digital Era' በሚል ርዕስ እና ሌሎች ሁለት የጥናት ወረቀቶች ቀርበዋል።
በመጨረሻም ለጥናቱ ተሳታፊዎች እና አስተባባሪዎች የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር እና የዩንቨርሲቲው ም/ፕሬዚዳንት የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/

Photos from Tourism Training Institute's post 28/04/2026

ስልጠና ከወሰዱት 139 የልምድ ባለሙያዎች 124 ያህሉ በጥሩ ውጤት አለፉ
ቱ. ማ. ኢ
ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ ጋር በመተባበር በምግብ ዝግጅት፣ በእንግዳ አቀባበልና በመስተንግዶ፣ በቤት አያያዝ እና በዳቦና ኬክ ዝግጅቶች ለአንድ ወር ያህል ስልጠና ሲሰጥ ቆይቶ ምዘና በመስጠት አጠናቋል።
የአጫጭር ስልጠና ዴስክ ኃላፊ አቶ ሰለሞን አሰፋ ስልጠናው በሥራ የተገኘን ዕውቀት አጫጭር ስልጠና ሰጥቶ በመመዘን ወደ ደረጃ ለመቀየር የሚያስችል ሲሆን ከ139 ሰልጣኞች መካከል 124 የሚሆኑት ተመዝነው በጥሩ ብቃት አልፈዋል ብለዋል፡፡ ምዘናውን ያላላፉ 15 የሚሆኑት ሰልጣኞች በቀጣይ ራሳቸውን በማብቃት ድጋሚ መመዘን የሚችሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ስልጠናውን ሲወስዱ የነበሩ ሰልጣኞች በልምድ ሲሰሩ ከነበረው በዘርፉ ባለሙያዎች የተሰጠው ስልጠና እጅግ እንደጠቀማቸው፤ ጉልበት ከሚያደክም ሥራ የተሻለ፣ ጊዜና ገንዘብ ሊቆጥብ የሚችል አሰራር እንደሰለጠኑም ገልጸዋል፡፡
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/

Photos from Tourism Training Institute's post 25/04/2026

ኢንስቲትዩቱ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ሚያዝያ 2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
የኢንስቲትዩቱ የጥናትና ምርምር ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም ኢንስቲትዩቱ እና ዩንቨርሲቲው አብረው ሲሰሩ እንደነበር አስታውሰው
በቱሪዝም እና በሆቴል ዘርፍ በስልጠና በጥናትና ምርምር እና የማማከር አገልግሎት የሚሰጥ አንጋፋ ተቋም መሆኑን እና
ከዩኒቨርሲቲው ጋር የተደረገው ስምምነት የተቋሙን ተልዕኮ በማከናወን ሂደት አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ በበኩላቸው የአማራ ክልልና በተለይም ባሕር ዳር ከተማና አካባቢው ያለውን እምቅ የቱሪዝም ሀብት በአግባቡ ለማልማትና ለመጠቀም ይህ ስምምነት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ገልጸው ፣ ለትግበራውም ዩኒቨርሲቲው ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።

ፊርማውን የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩምና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ ፈርመውታል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/

Want your university to be the top-listed University in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address

Near Guenet Hotel
Addis Ababa
4350