WMCC

WMCC

Share

AddisWalta - AW
አዲስ ዋልታ
Walta Media and Communication Corporate Who We Are
Walta Media and Communication Corporate S.C.

Photos from WMCC's post 13/04/2026

ኢራን በየትኛውም ማስፈራሪያና ዛቻ አትንበረከክም - የሀገሪቱ ፓርላማ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን ወደቦች ከዛሬ ጀምሮ እንደሚዘጉ ይፋ አድርገዋል፡፡

አሜሪካና ኢራን የመካከኛው ምስራቅ ጦርነትን ለማስቆም ከ47 ዓመታት በኋላ በፓኪስታን ያካሄዱት የፊት ለፊት የሰላም ውይይት ያለስምምነት መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡

ይህን ተከትሎም ፕሬዚዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ የሚወሰደው ሁለንተናዊ ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡

ከዛሬ ጀምሮም በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የሚከናወንን የመርከብ እንቅስቃሴ እንደሚያግዱ ገልጸው ÷ ለዚህም የሜሪካ ጦር ዝግጁ ነው ብለዋል፡፡

የፕሬዚዳንቱን ማስጠናቀቂያ ተከትሎም የዓለም የነዳጅ ዋጋ በድጋሚ በበርሜል ከ100 ዶላር በላይ ማሻቀቡን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

የኢራን ፓርላማ አፈ ጉባዔ ሞሃመድ ባጋር ጋሊቢፍ በበኩላቸው ÷ቴህራን አሜሪካ በየጊዜው በምታስተላልፈው የትኛውም ዘቻ እና ማስፈራሪያ እጅ አትሰጥም ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

የኢራን አብዮታዊ ዘብ ወደ ሆርሙዝ ወሽመጥ የሚጠጉ የጦር መርከቦች ላይ አስፈላጊውን ርምጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ላይ ይገኛልም ነው ያሉት፡፡

ሀገራቱ በዓለም ቁልፍ የነዳጅ መተላለፊያ መስመር በሆነው ሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የገቡበት እሰጣገባም በዓለም የተፈጠረውን የነዳጅ ቀውስ ይበልጥ እንዳያባብሰው ተሰግቷል፡፡

በመላኩ ገድፍ

Photos from WMCC's post 13/04/2026

ፋና መድረክ!

የሀገርን ሁለንተናዊ መልክ በሚወስኑ ርዕሰ ጉዳዮች የሚያደርገው የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ቀጥሏል!

‎ርዕሰ ጉዳይ፡- የቋንቋ እና ባህል ፖሊሲ

‎በተጠቀሰው ርዕሰ ጉዳይ ተከራካሪ ፓርቲዎች ኢትዮጵያ ሊኖራት የሚችለው የስራ ቋንቋ ብዛትና አይነት፣ እንደ ሀገር ብሔራዊ ቋንቋ ይኑር ወይንስ አይኑር፣ የትምህርት ስርዓቱ በምን ቋንቋ ይሁን? በሚሉና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ፖሊሲያቸው ተዳስሰዋል።

በዚህም፡-
👉‎ብልጽግና ፓርቲ
👉‎ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት
👉‎የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
👉‎ሕዳሴ ፓርቲ የፖሊሲ አማራጫቸውን አቅርበዋል።

ባቀረቡት የፖሊሲ አማራጭም በፋና መድረክ ተሞግተዋል፤ የሌሎች ፓርቲዎችን አማራጭ ሃሳብም ሞግተዋል።

‎አርብ ምሽት በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ቴሌቪዢንና በማሕበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይጠብቁን!

13/04/2026

ማንቼስተር ዩናይትድ ከሊድስ ዩናይትድ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ በኦልድትራፎርድ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ሊድስ ዩናይትድን ያስተናግዳል።

ሊጉ ለሀገራት ጨዋታ ከመቋረጡ በፊት የመጨረሻ መርሐ ግብሩን በአቻ ውጤት ያጠናቀቀው ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ ድል ለመመለስ ከበርካታ ቀናት በኋላ ወደ ሜዳ ይገባል።

ያለፉትን አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ ማሸነፍ ያልቻለው ተጋጣሚው ሊድስ ዩናይትድ በበኩሉ÷ ወደ አሸናፊነት ለመምጣት ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ሁለቱን ሲያሸንፍ በሦስቱ አቻ ተለያይተዋል።

ትናንት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ ቼልሲን 3 ለ 0፣ ሰንደርላንድ ቶተንሃም ሆትስፐርን 1 ለ 0፣ ክሪስታል ፓላስ ኒውካስል ዩናይትድን 2 ለ 1 ሲያሸንፉ፣ አስቶን ቪላ ከኖቲንግሀም ፎረስት 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት መለያየታቸው ይታወቃል።

ሊጉን አርሰናል በ70 ነጥብ ሲመራው ማንቼስተር ሲቲ በ6 ነጥብ ዝቅ ብሎ ይከተላል።

ማንቼስተር ዩናይትድ በ55 ነጥብ 3ኛ እንዲሁም አስቶንቪላ በተመሳሳይ 55 ነጥብ በግብ ክፍያ አንሶ 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

በወንድማገኝ ጸጋዬ

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

https://www.fanamc.com/, https://x.com/fana_arabic

Address

Addis Ababa