Ethio Lij

Ethio Lij

Share

PEACE FOR ALL!

Photos from Ethiopian Federal Police's post 20/07/2025

Ethiopian Federal Police

17/07/2025

ከምን ጋር የዋለች ምን . . . . ምን ተምራ ገባች አሉ!

ጀዌ-ቀዌ ወደ #መንደር አክቲቪስትነት ከወረደ ወዲህ አዋዋሉ ተቀይሮ ይሆን አይታወቅም ጨዋታዉ ሁሉ እንጨት #እንጨት ይላል። በዚህ ሰሞን እርሻ ዉስጥ ነበር በቆሎ ሲለቅም ፥ ዛሬ ደግሞ ወጣ ብሎ IMF ጋር ሄዷል። ከየት እንዳመጣት የማትታወቅ አንድ መረጃ ይዞ ሲንከወከዉ ነዉ የዋለዉ ።

ጀዌ እንደ ጦር የሚፈራዉን #አብይን ለማጥላላት የለጠፋት ልጥፍ አብይን የምታስተዋዉቅ እንደሆነች ግን አልተረዳዉም መሰለኝ ። የዉጭ ሀገር እርዳት ከ 12% ወደ 4% #አሽቆልቁሏል ያለባት አባባል የአብይ ስኬት መሆኑን የሚነግረዉ ጠፍቶ ነዉ? #እርዳታ አይቀንስ ነዉ ወይስ እየለመንን እንኑር ነዉ ጉዳዩ ? 😅

አይ ጀዌ ቀዌ . . . ምነዉ ለሩቶ የተኑስት እዛዉ በከበቡሽ እና ባስጨነቁሽ

16/07/2025

የJWF አራማጁ #ጀዋር አብይ አህመድ ያወራው አይደለም የተነፈሰው፤ የሰራው አይደለም ያለመው እንቅልፍ ይነሳዋል፤ የውሸት ማሽን ሆኖ ያልተፈጠረን እንደተፈጠረ የማድረግ ክፉ አባዜ ቀንና ሌት ያስቃዥዋል....
#አጋልጥ

16/07/2025

#ከ IMF እስከ ማሳ የቀጠለው የጀዋር ውሸቶች!!

16/07/2025

Photos from Ethio Lij's post 15/07/2025

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰብሳቢነት እየተካሄደ የሚገኘው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2018 ዓ.ም ሀገራዊ እቅድ ግምገማ በምስል፡-

Photos from Ethio Lij's post 14/07/2025

በ2017 የሥራ ዘመን ትርጉም ያለው እና ለመጪው የ2018 የቀጠለ የእድገት ጉዞ ጠንካራ መሠረት የሚሆን እድገት ፈፅመናል። በዚህ መነሻም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለመጪው ዓመት ለትግበራ የተዘጋጀውን የ2018 የተሟላ የሁሉም ዘርፎች እቅድ እና ሀገራዊውን የልማት እቅድ ለመገምገም ተሰብስቧል።

ከግምገማ እና ውይይታችን ጎን ለጎንም የአረንጓዴ ዐሻራችንን አሳርፈናል።

14/07/2025

የማይረሳ ቁስል፡ የሻዕብያ ወረራ በትግራይ ያስከተለው መዘዝ

የ2013 ዓ.ም. በዓይኔ ፊት ድቅን ይላል። የሻዕብያ መረማሸት በትግራይ ምድር ላይ ያሳደረው የጥፋት ዱካ ለዘመናት ከማስታወሻችን የማይፋቅ ጥቁር ጠባሳ ነው። ወገኔ ላይ የደረሰው ግፍ፣ በአክሱም፣ በአድዋና በየገጠሩ የታየው እልቂት፣ እህቶቻችንና ልጆቻችን ላይ የደረሰው በደል... ይህ ሁሉ ሲታሰብ ልብ ይደማል። ያን ዘመን መቼም አንረሳውም። የኖርንበትን ቤት ሲዘረፍ፣ ያፈራነውን ሲወድም፣ የሚበላው ሲያጣ መኖር ምንኛ ከባድ እንደነበር እኛ የትግራይ ልጆች እናውቀዋለን።

ይህ ቁስል በውስጣችን ዘላለማዊ ጥላቻን አኑሯል። ከጎናችን የቆመ፣ ለነፃነታችን የታገለ የሚባልልን ህወሓት ከዚህ ከፋፋይና በደለኛ ኃይል ጋር ሲተባበር ማየት እጅግ አሳምሞናል። ሻዕብያ በደማችን የረከሰ እጁን ይዞ እንዴት የኛ መሪ ሊሆን ይችላል? "ፅምዶ" የሚሉት ጥምረት ለእኛ የትግራይ ልጆች እንደ መርዛማ እባብ ነው የምንቆጥረው። የደረሰብንን መከራ ሳንረሳ እንዴት ከገዳዮቻችን ጋር እንቆማለን? ይህ ቁስል ዘላለማዊ ነው፣ ጥላቻውም እንዲሁ። የትግራይ ህዝብ ይህንን በደል በልቡ ቀርጾ ለትውልድ ያስተላልፋል። ለወደፊትም ማንነታችንንና ፖለቲካችንን የሚወስን ትልቅ ምዕራፍ ሆኖ ይቀጥላል።

Photos from Ethio Lij's post 14/07/2025

ህይወት አድን ስራ በፈጣሪም በሰዉም ዘንድ ትልቅ ዋጋ አለዉ።

ዛሬ ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከ170 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለኩላሊት ህሙማን 20 የዲያሊሲስ ማሽን እና 10 ዘመናዊ አልጋዎችን በማቅረብ ለ180 ታካሚዎች ለ3 አመት የሚሆን የዳያሊስስ ግብዓቶች ከወንበሮች ጋር አስረክቦናል።

ከፍለዉ መገልገል ለማይችሉ 144 ታማሚዎች በምኒልክ ኮምፕሬሄንሲቭ እና ዘዉዲቱ ሆስፒታሎች በየአመቱ እስከ 25 ሚሊየን ብር በመመደብ የዛሬ አምስት ዓመት ያስጀመርነዉ ነፃ የኩላሊት እጥበት አገልግሎት ላይ የዛሬዉ ድጋፍ ሲጨመርበት አገልግሎቱን በእጥፍ ለማሳደግ ስለሚያስችለን ለታካሚዎቻችን ትልቅ እፎይታ ነው።

የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕን በህሙማን፣ በከተማ አስተዳደሩ እና በራሴ ስም እጅግ አድርጌ እናመሰግናለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ

Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ

Photos from Ethio Lij's post 14/07/2025

2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የትጋትና የስኬት ዓመት ነበር - አቶ አደም ፋራህ

ዛሬ ሀምሌ 07/2017 ዓ.ም የብልፅግና ፓርቲ የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲ ስራዎች ማጠቃለያ የግምገማ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህ ወቅት የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ እንደገለፁት 2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የትጋትና የስኬት አመት ነበር።

ፓርቲውን በሰብዓዊና በቁሳዊ ሀብት ማጠናከር፤ በዘመናዊ መረጃ ማደራጀት፤ ዲጂታል ብልፅግና እውን ከማድረግና ገዥ ትርክትና ቅቡልነት ከማረጋገጥ አኳያ በትጋት የተከናወኑ ስራዎች ስኬታማ ናቸው ብለዋል።

በአስተሳሰብ፤ በአደረጃጀትና በአሰራር የተዋሃደ ፓርቲ ለመፍጠር የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ እንደነበሩ የተናገሩት አቶ አደም ፋራህ፥ በዚህም የፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ እና አምስተኛ ዓመት ምስረታ በዓል በተቀናጀና በተናበበ መንገድ መሳካት ችሏል ነው ያሉት።

የሀገራችንን የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነትና ዘላቂነት ያለው እንዲሆን በትኩረት ተሰርቷል በዚህም አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ህዝቡን በማሳተፍ በተቀናጀ መንገድ መስራት በመቻሉ በአገራችን አንፃራዊ ሰላም መስፈን እንደቻለ ተናግረዋል።

በንቅናቄ የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ ያወሱት ም/ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ፥ ከተረጂነት ለመውጣት የተከናወኑ ስራዎች የሀገራችንን የተረጂነት ታሪክ ለመቀየር መሰረት የጣሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ምክትል ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው እንደጠቀሱት ህዝቡ አካታችች ሀገራዊ ምክክር ላይ እንዲሳተፍ መሰራቱን አመላክተዋል፤ በዚህም አካታች ሀገራዊ ምክክር ሂደት በተሳካ መንገድ እንዲቀጥል ተደርጓል ብለዋል።

ገዥ ትርክትና ቅቡልነት እንዲረጋገጥ በመሰራቱ ሀገራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ አዎንታዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል።

በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ድሎችን ማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በመቅረፍ ለሁለንተናዊ ብልፅግና መረጋገጥ ህዝብን በማሳተፍ መስራት ይገባል ብለዋል።

14/07/2025

Addis Ababa Corridor Development

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address

Addis Ababa