Z mike Digital
"A full-service digital marketing and advertising agency, delivering results with targeted strategies in SEO, social media, and online ads.
How to create animated video
#የመሠረት ዜና ለ650 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሲደርስ የነበረ የምግብ እርዳታ ሊቆም መሆኑ ተሰማ
(መሠረት ሚድያ)- የአለም ምግብ ፕሮግራም (World Food Programme) 10 ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ርሀብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ችግር አጋጥሟቸው እንደሚኝ ገልፆ ይህ እየሆነ ባለበት ወቅት በገንዘብ እጥረት ምክንያት ለ650 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሲያደርስ የነበረውን የምግብ እርዳታ ሊያቆም መሆኑን ዛሬ አስታውቋል።
ከእነዚህ መሀል 3 ሚልዮን የሚሆኑት በጦርነት እና በከባቢ አየር ጠባይ መቀየር ምክንያት ተሰደው የሚገኙ መሆናቸውን የጠቆመው ይህ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አካል የሆነ ተቋም 4.4 ሚልዮን የሚሆኑ እርጉዝ እና አጥቢ እናቶች እንዲሁም ህፃናት በከፍተኛ ደረጃ ለረሀብ ተጋልጠው ይገኛሉ ብሏል።
"በኦሮሚያ፣ ሶማሌ፣ ትግራይ እና አፋር የህፃናት በምግብ እጥረት መዳከም ተከስቷል" ያለው የአለም ምግብ ድርጅት በኢትዮጵያ እና በቀጠናው ባሉ ሀገራት ያሉ ግጭቶች ችግሩን እያባባሱ እንደሚገኙ ይፋ አድርጓል።
ይህም አልበቃ ብሎ በመጪዎቺ ወራት በደቡብ-ምስራቅ ኢትዮጵያ ዝቅተኛ የዝናብ መጠን የተተነበየ ሲሆን ይህም በሶማሌ ክልል ድርቅ እንዳያስከትል እንደተፈራ ጨምሮ ገልጿል።
በአማራ ክልል የቀጠለው ግጭት፣ የእርዳታ እህል የጫኑ ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈፀም ዝርፊያ መሬት ላይ ያሉ ችግሮች ተብለው በዛሬው መግለጫ ላይ የተነሱ ሲሆን የአለም አቀፍ እርዳታ መቀነስ በዋናነት ተጠቅሷል።
"አዲስ እርዳታ ካልተገኘ በቀር ለ3.6 ሚልዮን ኢትዮጵያውያን የምናቀርበውን እርዳታ በመጪዎቹ ሳምንታት ለማቋረጥ እንገደዳለን፣ አሁን ላይ ለ650 ሺህ ሰዎች ስናደርስ የነበረውን የነፍስ አድን እርዳታ እያቆምን ነው" ብሏል በመግለጫው።
ይህ አሳሳቢ ክስተት እንደ ቢቢሲ እና አልጀዚራ ባሉ አለም አቀፍ የሚድያ ተቋማት ሽፋን ቢያገኝም አንድም የመንግስት ሚድያ እስካሁን እንዳልዘገበው መሠረት ሚድያ ተመልክቷል፣ በመንግስት አካላትም የተሰጠ መግለጫ የለም።
ኢትዮጵያ ስንዴ ከራሷ ተርፎ ለውጭ ሀገራት መላክ እንደጀመረች ተደጋግሞ ቢገለፅም በርካታ ሚልዮን ዜጎች ርሀብ አጋጥሟቸው እንደሚገኙ የአለም አቀፍ ተቋማት መረጃዎች ያሳያሉ።
መረጃን ከመሠረት!
#የመሠረት ዜና ኬንያ ዘንድሮ የምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት እንደምትሆን አይ ኤም ኤፍ ጠቆመ
(መሠረት ሚድያ)- በያዝነው የፈረንጆቹ 2025 ዓ/ም የኬንያ ኢኮኖሚ ከኢትዮጵያ እንደሚበልጥ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (International Monetary Fund- IMF) ያወጣው የአመቱ የኢኮኖሚ እድገት ትንተና ያሳያል።
ኢትዮጵያ ካለፉት ጥቂት አመታት ወዲህ በምስራቅ አፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት ሆና የነበረ ቢሆንም በቅርቡ በመንግስት ይፋ የሆነው እና በእነ IMF የተደገፈው ብርን የማዳከም ሂደት የኢኮኖሚውን የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እና አገልግሎት ዋጋ (GDP) በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንስ ማድረጉ ታውቋል።
በዚህም መሰረት የኬንያ GDP 132 ቢልዮን ዶላር ሲሆን በብር መዳከም ምክንያት በብዛት ከአምናው የቀነሰው የኢትዮጵያ GDP ደግሞ 117 ቢልዮን ዶላር እንደሚሆን IMF እንደተነበየ መሠረት ሚድያ ተመልክቷል።
ኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘቧን በማዳከሟ ብር ከ55 ፐርሰንት በላይ ዋጋውን እንዳጣ የሚታወስ ሲሆን ሀገሪቱ ይህን በማድረጓ ከ IMF 3.4 ቢልዮን ዶላር ገደማ ብድር እንደተፈቀደላት በወቅቱ ተነግሮ ነበር።
የብር ዋጋ መዳከም በተጨማሪም ሀገሪቱ ከውጭ አበዳሪዎች ጋር ያለባትን 28.9 ቢልዮን ዶላር ብድር ለማስተካከል እንዳገዘ ብሉምበርግ ዘግቧል።
የብር መዳከም የ GDP መቀነስ ብቻ ሳይሆን በተለይ ከውጭ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ምርቶች ላይ ከፍተኛ ጭማሪ ማስከተሉ ይታወቃል።
በተቃራኒው የኬንያ መንግስት በርካታ የውጭ ብድር ያለበት ቢሆንም የሀገሪቱ መገበያያ ሽልንግ ከአምናው ጋር ሲነፃፀር በ21 ፐርሰንት መጠንከሩ ታውቋል፣ የኢኮኖሚው መረጋጋት እና በርካታ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ዘርፎች መኖራቸውም ለኢኮኖሚው መጠንከር አስተዋፅኦ ማርረጋቸው ተጠቅሷል።
መረጃን ከመሠረት!
Click here to claim your Sponsored Listing.
Website
Address
000