Ever Light
Updates on different situations You can get what you want,if you put here.
የጠነከረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙት፣ ጥብቅ ወዳጅነት።
01/05/2026
🇪🇹⚡️ ከነዳጅ ጥገኝነት ወደ አረንጓዴ ኢነርጂ!
ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሽግግር የአህጉራችን ፋና ወጊ ሆና ቀጥላለች። ይህ ጉዞ የት ደረሰ? ቁልፍ ስኬቶችንና የወደፊት ግቦችን ቀጥሎ ባለው መረጃ እንቃኝ።
🚫 ታሪካዊ ውሳኔ (2016)
ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ በመከልከል ከአፍሪካ የመጀመሪያዋ ሀገር በመሆን ታሪክ ሰርታለች። የዚህ ውሳኔ ዓላማው በውጭ ምንዛሪ የሚገዛውን የነዳጅ ወጪ ሸክም መቀነስና አካባቢን መጠበቅ ነው።
🚗 የቁጥሮች እድገት በ2017፦
100,000 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ ስራ ገብተዋል። በአዲስ አበባ ብቻ በቀን 90,000 መንገደኞችን በንፁህ ኢነርጂ በማጓጓዝ ላይ ይገኛሉ።
በ2018፦ ቁጥሩ ወደ 140,000 ከፍ እንዲል ታቅዶ በስፋት እየተሰራበት ነው።
🏭 የ2023 ራዕይ፦
ኢትዮጵያ የራሷን የኤሌክትሪክ መኪኖች በመገጣጠም እና በመላ ሀገሪቱ ከ400 በላይ የቻርጅ ማደያዎችን በመገንባት፣ በ2023 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ቁጥርን 500,000 ለማድረስ በትጋት እየሰራች ትገኛለች።
ይህ ለውጥ ለሀገር ኢኮኖሚ ካለው ፋይዳ ባሻገር ለነገው ትውልድ ንፁህ አየርና የተስተካከለ የአየር ንብረት ለማስረከብ ትልቅ እርምጃ ነው።
እናንተስ ምን ትላላችሁ? የወደፊቱ ትራንስፖርት በኤሌክትሪክ መሆኑን ይደግፋሉ? አስተያየትዎን በኮሜንት ያጋሩን! 👇