EthioTimes

EthioTimes

Share

EthioTimes is a source of credible news and entertaining TV and radio productions.

Photos from EthioTimes's post 07/16/2026

በሀገራችን የኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ትልቁ ውጤት በደቡብ ኮሪያ ተመዘገበ‼️

በደቡብ ኮሪያ ጊምቺዮን ከተማ ከሐምሌ 3_6/2018 ዓ.ም.(July 10_13/2026) የዓለም ሻምፒዮና(በWorld Championship In South Korea # Gimcheon City)

ከ46 ሀገራት የተወጣጡ ከ2000 በላይ አትሌቶች የተሳተፉበት በደቡብ ኮሪያ በተዘጋጀው የአለም ሻምፒዮና ውድድር ላይ ወደ ቦታው ያቀናው የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ብሔራዊ ቡድን ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ ደምቆ አጠናቀቀ።

በኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ማስተር ኤልያስ ኩመል እየተመራ ወደ ቦታው ያቀናው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በተሳተፈባቸው ውድድሮች ሁሉ የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ በመግባት የሀገራችንን ስም በአለም አደባባይ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ማድረግ መቻላቸው ተሰምቷል።

ከአምስት ወር በላይ ዝግጂት ሲያደርግ የቆየው እና ወደ ቦታው ያቀነው ቡድናችን በውድድሩ ላይ የጠበቅነውን ውጤት በማምጣታችን ደስ ብሎናል ያሉት የቡድኑ አሰልጣኝ እና ቡድን መሪ ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ማስተር ኤልያስ ኩመል ውድድሩ ግን አድካሚ እንደነበረም ገልፀዋል።
አክለውም ብሔራዊ ቡድናችን በአራት ተወዳዳሪዎች በኢንተርናሽናል እና በኮፖት ቴኳን-ዶ የውድድር አይነቶች የተወዳደረ ሲሆን ሁሉም በተወዳደሩበት ካታጎሪ ሜዳሊያ ውስጥ በመግባት በጥሩ ውጤት ማጠናቀቅ መቻላቸውን አብራርተዋል።
በውድድሩ ላይ ሁለት ወርቅ: ሶስት ብር እና አራት ነሀስ በአጠቃላይ ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በቀን 7/11/2018 ዓ.ም ጠዋት 2:00 ሰዓት ወደ ሀገራቸው የተመለሱ ሲሆን ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱም በአርቱ ደጋፊዎች በኩል ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

በደቡብ ኮሪያ በተዘጋጀው የአለም ሻምፒዮና ውድድር ላይ ወደ ቦታው ያቀናው የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ብሔራዊ ቡድን ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ ደምቆ ከማጠናቀቁ ባሻገር የሁለቱን ሀገራት የቆዬ በጎ ግንኙነት ከፍ እንዳደረገ ተነግሯል።

በጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ

Photos from EthioTimes's post 07/16/2026

በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ አርጀቲና እና ስፔን ለፍጻሜ ደረሱ።

ከእንግሊዝ ጋር ለዋንጫ ለማለፍ የተጫወተችው አርጀንቲና እስከ 85ኛው ደቂቃ ድረስ 1 ለ 0 ብትመራም ድራማዊ በሆነ መንገድ 2 ጎል አግብታ 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ፍጻሜው ጨዋታ አልፋለች።

ለተከታታይ ሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ተጋጣሚ የሆነችው አርጀንቲና የፊታችን እሁድ ምሽት 4:00 ፈረንሳይን ጥላ ወደ ፍፃሜ ካለፈችው ስፔን ጋር ትጫወታለች።

Via- tikvahethiopia

Want your business to be the top-listed Media Company in Silver Spring?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address

Silver Spring, MD

Opening Hours

Monday 9am - 5pm
Tuesday 9am - 5pm
Wednesday 9am - 5pm
Thursday 9am - 5pm
Friday 9am - 5pm
Saturday 9am - 5pm
Sunday 9am - 5pm