AAU - Muslim Students Union

AAU - Muslim Students Union

Share

The Official Page of AAU - MSU

Telegram: t.me/aaumsu
Twitter: twitter.com/aaumsu12

15/03/2026

ጥያቄዎቻችን ምን ምን ናቸው?

1) በመመሪያ የተከሰከሰው የሙስለም ተማሪዎች ሒጃብ (ኒቃብ) በመመሪያ አውቅና ይሰጠው፡ መሠል የመብት ጥሰቶች ሲፈፀሙ የሚቀጣ ድንጋጌም ይውጣ፤

2) ከጁምዓ የሶባት ሰዓት ጀምሮ አስከ ተራዊህ አና ተሐጁድ ድረስ ሴሚስቴር በሴሚስቴር፡ አመት በአመት ጭቅጭቅ አየተነሳ ስለሆነ ያንን የሚቀርፍ አወቃቀር ይዘርጋ፤

3) ላለፋት 18 ወሪት ጨቋኙ መመሪያ መውጣቱን ተከትሱ በደል ለደረሰባቸው ሙስሊም ተማሪዎች ካሳ ይሰጥ፤

4) ባለፋት 18 ወራት ጨቋኝ መመሪያን ከማውጣት ጀምሮ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በደል ሲፈፅሙ የነበሩ የዩኒቨርሲቲው አካላት ተጠያቂ ይሁኑ፤

5) ለለፋት ጊዜያቶች በዩኒቨርሲቲው አመራሮች አናውቅህም በመባል ሕውናው ለተገፈፈው መስለም ተማሪ እና ተወካዮቹ አውቅና ይሰጥ፤

6) ስለ ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ በማንሳታቸው ብቻ በዩኒቨርሲቲው ክስ የተመሰረተባቸው ተማሪዎችን ዩኒበርሲቲው በይፋ ይቅርታ ይጠይቅ፤

7) በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚሰሩ መሰረተ ልማቶች ኒቃብ የሚለብሱ ሴት ሙስሊም ተማሪዎችን ባገናዘበ እና ባካተተ መልኩ ይሁን።

ጥያቄዎቻችን አነኚህ ናቸው፡፡ አስቸኳይ አና ፍትሐዊ መልስ እንፈልጋለን። አስቸኳይ እና ፍትሐዊ መልስ አስኪመጣ ድረስ አንጠይቃን። አስፈላጊ በሆነው መንገዱ ሁሉ። ዛሬም ነገም፤ ቢሮም በአደባባይም፤ በሁሉም ጊዜ በሁሉም ቦታ እንጠይቃበን ፤ ጥያቄ አለን አንላለን።

Want your place of worship to be the top-listed Place Of Worship in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Address


Addis Ababa