Defence Construction Design Enterprise - DCDE

Defence Construction Design Enterprise - DCDE

Share

Defence Construction Design Enterprise mainly engaged in building & road design, and consulting.

Photos from Defence Construction Design Enterprise - DCDE's post 08/09/2023

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት የሥራ አመራሮችና የሥራ ኃላፊዎች የመከላከያ ስፔሻይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልን ጎበኙ፡፡

ጳጉሜ 2 ቀን 2015 ዓ.ም (የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት) በዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር መርዕድ ታዬ የተመራው የድርጅቱ አመራሮችና የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በቢሾፍቱ ከተማ ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የመከላከያ ስፔሻይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ጎብኝተዋል።

የሆስፒታሉ ጠቅላላ ዲዛይን ሥራ በመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት ተሠርቶ ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚኘው ይህ ሆስፒታል በቢሾፍቱ ከተማ አጠቃላይ ስፋቱ 76,560 ካሬ ሜትር የተንጣለለ ግቢ ውስጥ በ29 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና በህክምናው ቴክኖሎጂ የተደረሰበትን አብዛኛውን ግብዓት ያሟላ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የሆስፒታሉ ኃላፊ ጀነራል ሸዋዬ ኃይሌ ታካሚዎች ለከፍተኛ ህክምና ውጭ ሀገር ድረስ በመሄድ የሚደርስባቸውን እንግልትና ከፍተኛ ወጭ የሚቀንስ እናም በአህጉር ደረጃ ተወዳደሪ የሚሆን የህክምና ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሆስፒታሉ ከፍተኛ ህክምና ከመስጠት ባሻገር የህክምና ግብዓቶችን በማምረት በሀገራችን የሚታየውን የግብዓት ችግር ለመቅረፍም ጭምር ታስቦ በዘመናዊ መንገድ የተገነባ መሆኑንም ጀነራል ሸዋዬ አሳውቀዋል፡፡

ሆስፒታሉ ቀድሞ ከሦስት አሥርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ አየር ኃይል አማካይነት በ1975 ዓ.ም ታቅዶ በ1982 ዓ.ም ግንባታው ተጀምሮ በወቅቱ በነበረው መጠን አገልግሎት መስጠት የጀመረ ቢሆንም በተፈላጊ ደረጃ አገልግሎት ሲሰጥ እንደቆየ ጠቅሰው ነገር ግን የተደራጀ ዘመናዊ ሆስፒታል እንዲሆን የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር ተረክቦ በ2000 ዓ.ም ዘመኑ የደረሰበትን የህክምና ደረጃ በሚያሟላ መልኩ የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ መጀመሩን፤ ጀነራል ሸዋዬ እና የግንባታ ፕረጀክት ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር አሸብር ተስፋዬ በሰጡት ማብራሪያ ገልጸዋል፡፡ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩንም ተናግረዋል፡፡

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር መርዕድ ታዬ የግንባታ ዘርፉ ጥራት እና ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን የዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎችን በበለጠ ትኩረት እና በአጋርነት ለመሥራት በድርጅታቸው በኩል ያለውን ከፍተኛ ዝግጁነት ገልጸው በጉብኝቱ ላይ ለተደረገው ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።

05/09/2023

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር "የውሃ ሀብታችን ለብልፅግናችን" በሚል መሪ ሐሳብ በሳይንስ ሙዚየም ያዘጋጀውንኤግዚቢሽን ጎብኝቷል (ነሐሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም) ።

የድርጅቱ አመራሮችና ሠራተኞች ኤግዚቢሽኑን ከመጎብኝት ጎን ለጎን ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ጋር በቀጣይ በአጋርነት አብሮ መሥራት በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ውይይት አድርገዋል።

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት የግንባታው ዘርፍ ጥራቱን እና ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን ዲዛይንና ቁጥጥር በማድረግ በሀገሪቱ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ትልቅ አሻራ በማሳረፍ የዳበረ ልምድ ያለው ድርጅት እንደመሆኑ ከተቋማት ጋር በአጋርነት ስለሚሠራ ቸው ሥራዎች ማብራሪያ ተሰጥቷል።

20/04/2023

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የኢድ -አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ::

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address


Kirkos Sub City
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30