ሸዋ Hub

ሸዋ Hub

Share

ሸዋ የትልቋ ኢትዮጲያ ማዕከልነቱን እንዳስጠበቀ ኅብረ ብሄራዊ ክልላዊ አስተዳደር ይዋቀራል፡፡

Photos from Multi Ethnic Shoa's post 07/03/2026

የበልበሊት እየሱስ ገዳም....!

ይህ ገዳም በእንሳሮና መረሐቤቴ መሀል፣ በጀማ ሸለቆ አቅራቢያ የሚገኝ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ በ152 ኪ.ሜ ከደብረብርሀን 105 ኪ.ሜ እንዲሁም ከለሚ ከተማ በ22 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።ገዳሙ ልዩ ጸጋዎችና ቅርሶች፡ሲኖሩት

የግብፅ ስደት መታሰቢያ፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በስደት ዘመን ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ካረፈባቸው 5 ገዳማት አንዱ እንደሆነ ይነገራል።

የተፈጥሮ ሀብት፡ አካባቢው ምንም እንኳን ደረቅ ቢመስልም፣ በገዳሙ ውስጥ ግን ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ሙዝና ሸንኮራ ከአመት አመት ይመረታል።

ሚስጥራዊ ዋሻዎች፡ አቡነ ዜናማርቆስ እና አቡነ ተክለኃይማኖት የጸለዩበት፣ እስከ እየሩሳሌም የሚያስኬድ መንገድ እንዳለው የሚታመንበት እና በ"ተርቦች" የሚጠበቅ አስደናቂ ዋሻ ይገኝበታል።

ፈዋሽ ጸበል፡ ከተለያዩ ህመሞች የሚፈውስ ጸበል እና በአቡነ ተክለኃይማኖት ዘንግ ፈልቆ ለመዋኛነት የሚያገለግል ገንዳ አለው።

28/02/2026

ልጅ ኃይለማርያም_ማሞ!!

ደጃዝማች ኃይለማርያም ማሞ በትውልድ ሃገራቸው ደብረብርሃን ሲሆን ከጣሊያን ፋሽስት ጋር በአንድ ቀን ውስጥ በአደረጉት እልህ አስጨራሽ ጦርነት 4 የጠላት መኪናዎችን በማቃጠል፣ 40 የፋሽስት ወታደሮችን በመግደል ትልቅ ታሪክ የሰሩ ዘመን የማይሽራቸው ጀግና ነበሩ፡፡

ሃገር አማን ብሎ ወደ መሀል ሃገር በሚተመው የፋሽስት ወራሪ ኃይል ላይ በደፈጣ ውጊያ ከፍተኛ ኪሳራ አደርሷል፡፡ በዚህም የተነሳ መጪው ዘመን ከጀግኖኞች አርበኞች ጋር ለፋሽስት ኢጣሊያ ጨለማ መሆኑን የተግባር መልዕክት እሰተላለፉ፡፡

ደጃዝማች ኃይለማሪያም ማሞ በአሥር ሰዓት ገደማ ላይ ከቤቱ ተነሥቶ ጫጫ ሱኬ ሴራቤ ከምትባለው ቀበሌ ምቹ ቦታ ይዘው ጠበቁት ፤ ጠላትም ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ አልፋለሁ ሲል አደጋ ጥለው አምስት ካሚኒዮኖች ሰብረው በውስጡ የነበሩትን አንድ መቶ አርባ የሚሆኑ የጠላት ወታደሮች ገድለው ሰባት ማረኩ፤ ከእነዚሁ ሁለት ሸሽተን እናመልጣለን ብለው ሲሞክሩ በጥይት ተመትተው ተያዙ፡፡

ይህ የደጃዝማች ኃይለማሪያም ማሞ ገድል የመንፈስ ጥንካሬ የዘራባቸው የሸዋ ጎበዛዝት ቀፎው እንደተነካበት ንብ በነቂስ ለምተመም አልዘገየም ነበር፡፡ ያላቸው ጥይትም ሆነ ስንቅ የሚያወላዳ ስላልነበረ ምሽግ ይዞ ከመዋጋት ይልቅ የደፈጣ ወጊያን ምርጫቸው አደረጉ፡፡

ጥሬ በቆሎ ቀርቀጭ እያደረጉ፣ ከወንዝ ውሃ እየተጎነጩ፣ በአንድ ቦታ ሳይረጉ ጣሊያንን በደፈጣ ውጊያ መግቢያ መውጪያ አሳጡት፡፡ ደጃዝማች ኃይለማርያም በጠላት ጦር ላይ ባደረሱት ተደጋጋሚ ጉዳት የፋሺስት ጦር ደጃዝማች ኃይለማርያምን ከዋነኛ ጠላቶቹ መካከል አንዱ አደርጎ እንዲፈርጃቸው ተገዷል፡፡

በደብረ ብርሃንና አካባቢው የነበረው የፋሺስት ጦር ደጃዝማች ኃይለማርያምን መደምሰስ ስላልቻለ በርካታ ወታደርና ትጥቅ ከሌሎች አካባቢዎች ለመውደስ ተገዶ ነበር፡፡ ጀግናው አርበኛ ደጃዝማች ኃይለማርያም ማሞ ግንቦት 28 ቀን 1930 ዓ.ም ቡልጋ ውስጥ በተደረገ ከባድ ጦርነት ላይ ህይወታቸው አለፈ።

👉የፋሺስት ጦር ከኢትዮጵያ ከተባረረ በኋላም ደብረ ብርሃን ከተማ ውስጥ በስማቸው ት/ቤት ተገንብቶላቸዋል፡፡

👉በአዳማ (ናዝሬት) ከተማ የሚገኝ ሆስፒታልም በስማቸው ተሰይሞላቸዋል፡፡ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥም በስማቸው የተሰየመ መንገድ ይገኛል፡፡

👉ከዚህ በተጨማሪም፣ 75ኛው የአርበኞች ድል መታሰቢያ ሲከበርም ከሌሎች 25 ታላላቅ አርበኞች ጋር በስማቸው የመታሰቢያ ቴምብር ታትሞላቸዋል፡፡

ለደጃዝማች ኃ/ማርያም ማሞ ጀብድና ጀግንነት ከተገጠሙ ግጥሞች መካከል…

ኃይለማርያም ማሞ የጦሩ ገበሬ፣
ይኸንን ሶላቶ ነዳው እንደበሬ።

መተኮሱንማ ማንም ይተሳል፣
ኃይለማርያም ማሞ አንጀት ይበጥሳል።

ሀይለማሪያም ማሞ የጦሩ ገበሬ፣
ፈረሱን እንደሰዉ አስታጠቀዉ ሱሬ፡፡

ኃይለማርያም ማሞ የጦሩ ገበሬ፣
እያላጋው መጣ ነጬን ከነጭ በሬ፡፡

ተብሎ ተገጥሞላቸዋል ።

Photos from Multi Ethnic Shoa's post 26/02/2026

ለስራ ፈላጊወች

የቅጥር ማስታወቂያዎች 👇

Photos from Multi Ethnic Shoa's post 25/02/2026

ሸዋ የደራሲያን፣ የአርበኞች፣ የነገሥታት መፍለቂያ!

ሸዋ ውስጥ በመሳፍንትነትና፣ በመኮንነት እያገለገሉ፣ በድርሰቱም የኢትዮጵያ ስነ- ጽሑፍ ከፍ አርገው እና ሀገርን በማቋቋም ትልቅ ሚና ያላቸው የሸዋ መሳፍንት እና መኳንት !

👉ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተ ወልድ
👉ጸሐፌ ትዕዛዝ ገብረ ሥላሴ
👉ተከለ ጻድቅ መኩሪያ
👉ከበደ ሚካኤል
👉አምባሳደር ከተማ ይፍሩ
👉መርስኤ ኃዝን ወለደ ቂርቆስ
👉ራስ መኮንን
👉አለቃ ኪዳን ወልድ ክፍሌ
👉አለቃ ዘነበ
👉መኮንን ሀብተ ወልድ
👉ዶ/ር ተፈራ ደግፌ
👉 ደስታ ተክለ ወልድ
👉ራስ ተሰማ ናደው
👉ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም
👉ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ
👉ጸሐፌ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ
👉ራስ አበበ አረጋይ
👉ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደ መድኅን
👉ራስ አባተ ቧ ያለው
👉ብላቴን ጌታ ማሕተመሥላሴ ወልደመስቀል
👉ደጃዝማች ተሰማ እርገጤ
👉ቀኝአዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ
👉አርበኞ ሸንቁጥ
👉ደጃዝማች ተሾመ ሸንቁጥ
👉ልጅ ኃይሌ ሸንቁጥ
👉ደጃዝማች አበበ ሸንቁጥ
👉ልጅ ይነሱ ሸንቁጥ
👉ልጅ ጥላሁን ሸንቁጥ
👉ደጃዝማች ሐብተሥላሴ በላይነህ
👉የዓለም ሎሬት መላኩ ወረደ
👉የዓለም ሎሬት ዶክተር አርቲስት አፈውርቅ ተክሌ
👉ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ
👉ራስ ደስታ ዳምጠው
👉ፊታውራሪ ገበየሁ
👉አርበኛ ሽዋረገድ ገድሌ
👉ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ
👉አርበኛ አስማረ ዳኜ

እነዚህ እና ሌላም በጀግንነታቸውና በድርሰታቸው ከፍተኛ የስነ ጽሑፍ ሚና ያላቸው እነ "ዳኛቸው ወርቁ" አሉ "አደፍርስ" በሚል ርእስ እስከ ዛሬ ድረስ ሕዝብን ያስደነቀ ነው።

በተለይ የኢትዮጵያን ታሪክ ለሕዝቡ በማሳወቅ ደረጃ "ተክለ ጻድቅና ብላቴን ጌታ ኅሩይ" ሁሌ በልባችን አሉ።

ሽዋ የሙህራንና የጀግኖች የነገሥታት መፍለቂያ።

✍️ Abreham Demeke

እናንተም ጨምሩበት🙏

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Website

Address


Addis Ababa
WWW.MULTIETHNICSHOA.COM