All In One Ethiopia

All In One Ethiopia

Share

Daily Business News in Ethiopia
Daily Job vacancy in Ethiopia
Daily Job vacancy in Ethiopia

28/09/2023

ላዳ መኪኖች በኢትዮጵያ ሊመረቱ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ላዳ መኪኖች በኢትዮጵያ ተመርተው ለአፍሪካ ገበያ ሊቀርቡ መሆኑ ተነገረ፡፡

የሩሲያዎቹን ላዳ መኪኖች በኢትዮጵያ ለማምረት የሚያስችል ሥምምነት መደረሱን ታስ የተሰኘው የሩሲያ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡

ከስምምነት ላይ የደረሰው አቭቶቫዝ የተሰኘው መንግስታዊው የቤት መኪና አምራች ኩባንያ መሆኑ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረቱት ላዳ መኪኖች÷ ሱዳንን፣ ደቡብ ሱዳንን እንዲሁም ኬንያን እና ሶማሊያን ጨምሮ ወደ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ይላካሉም ተብሏል፡፡

መኪኖቹን በቅርብ ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ውስጥ ማምረት እንደሚጀመር የተጠቆመ ሲሆን፤ ሌሎች የሩሲያ መኪና አምራች ኩባንያዎችም በኢትዮጵያ የመኪና መገጣጠም ዘርፍ ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እያሳዩ እንደሆነ መሆናቸው ተጠቁሟል።

በጉዳዩ ላይ ሁለት የሩሲያ መኪና አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ለመሥራት እየመከሩ መሆኑም ተገልጿል፡፡

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address


Jamo
Addis Ababa
45