yonas.com
YGG
04/06/2025
አነበብኩት ላካፍላችሁ
ንጉሡ በከተማው የሚገኝ ከሁሉ የሚበልጠውን ሊቅ እንዲያመጡለት ባለሟሎቹን አዘዘ። ባለሟሎቹን በጥበቡ፣በበማስተዋሉም እጅግ የላቀ የሚሉትን ጠቢብ አመጡለት።ንጉሡም ወደ ጠቢቡ እየተመለከተ "ሶስት ጥያቄዎች እጠይቅሃለሁ የመጀመሪያው ጥያቄዬ እግዚአብሔር የት ነው የሚኖረው?"
ጠቢቡም እጅ ነስቶ ይህን ጥያቄ ለመመለስ ትኩስ ወተት እና ስኳር ያስፈልገኛል አለ።ንጉሡም እንዲመጣለት አደረገ። ጠቢቡም ስኳሩን ወተት ውስጥ ጨምሮ አማስሎ ለንጉስ ሰጠው እንዲቀምሰው
"ግርማዊነቶ ወተቱ እንዴት ያለ ጣዕም አለው?" አለው
ንጉሱም"ይጣፍጣል"አለው
ጠቢቡም መልሶ"ከወተቱ ውስጥስኳሩን ማየትይቻላል? "ብሎ ጠየቀው
ንጉሱም"አይቻልም ስኳሩ ሟምቷል።"አለው
ጠቢቡም "ልክ እንደሟሟው ስኳር እግዚአብሔር ሁሉም የአለም ስፍራ ላይ አለ አናየውም እንጂ"አለው
ንጉሡ በመልሱ ረክቶ ሁለተኛው ጥያቄ ጠየቀው"ፈጣሪን እንዴት ልናገኘው እንችላለን?"
ጠቢብም ግርማዊነቶ ይህንን ለመመለስ የወተት ክሬም ያስፈልገኛል አለ። ንጉሡም እንዲያመጡለት አዘዘ።
ጠቢቡም እጅ ነስቶ"ግርማዊነቶ በክሬሙ ላይ በቅቤ ይታያል?"ብሎ ጠየቀው
ንጉሡም"ክሬሙን ብንናነሳው ቅቤ ከስር እናገኛለን ከላይ ግን አይታይም "አለው
ጠቢቡም"የሁለተኛ ጥያቄዎም መልስ እንዲህ ነው ፈጣሪም በእውነተኛ ማንነታችንን ወደ ልባችንን ስንመለስ እናገኘዋለን"አለው።
ንጉሡም በጠቢቡ ተደንቆ ወደ መጨረሻው ጥያቄ አለፈ"እግዚአብሔር ምን ማድረግ ይቻለዋል? "አለው
ጠቢቡም ከንጉሡ ሎሌዎች አንዱ እንዲቀርብለት ጠየቀ። ንጉሡም አስጠራለት። ጠቢቡም"ይህ ጠባቂዎ ንጉሠ ነገሥት ነው እንበል እናም ግርማዊነቶ ለንጉሥ ዙፋን ይገባዋል እና እርሶ ከእኔ ለጎን ይቆማሉ ጠባቂዎ ደሞ በዙፋኖ ይቀመጣል "አለ
ንጉሱም በመስማማት ዙፋኑን ለሎሌው ለቀቀ።
ጠቢቡ ወደ ንጉሡ እያየ" ፈጣሪ ሎሌን ጌታ፤ጌታን ሎሌ ማረግ ይችላል"አለው።
***
ብልሃት እና ጥበብን ስለሚወዱ ነገሥታት ምን ታስባላችሁ በጥበቡ የምታውቁትስ ምሳሌ የሚሆን ንጉሥ ማን ነው?
ማንበብ መልካም ስብዕና ያላብሳል 📚
https://t.me/joinchat/q4
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the organization
Website
Address
Addis Ababa