Erta'ale Media

Erta'ale Media

Share

Media company

27/11/2020

⬆️
ትህነግ ለውሸት ድምሰሳ 21ኛ ክ/ጦርን ለምን መረጠ?

በአበበ ሰማኝ (ከአዲ-ቀይህ) ህዳር 17 ቀን 2013 ዓ.ም

ከምስረታው ጀምሮ ምንም አይነት ሰብዓዊነት ያልፈጠረበት ትህነግ ለበርካታ አመታ የውሸት ካህን ሆኖ በህዝቦች ዘንድ መጠራጠርን፥ ኢትዮጵያን መካድን ለትውልድ አውርሶ በመቃብሩ ጫፍ ላይ ዛሬም እንደትናንቱ በተሰፋበት የሃሳዊነት አኮፋዳ ቱሪናፋውን ይለቃል።

ሰሞኑን የትህነግ የውሸት ቱቦ ማፍሰሻ ጌታቸው ረዳ በበቀቀኑ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርቦ ትርጉም በሌለውና ውጤት አልባ ሆኖ በትህነግ የፖለቲካ ሴራ በተሸረበው ነገር ግን ውስጡን ያላውቁት ቆራጥ የህዝብ ልጆች ለድንበራቸው መከበር ዋጋ በከፈሉበት የሻዕቢያ ጦርነት ታላቅ ገድል የፈፀመችው 21ኛ ክ/ጦር ሙሉ በሙሉ ደምስሰናታል ብሏል ።

ለመሆኑ ትህነግ ኢትዮጵያችን ካሏት ጀግና ክ/ጦሮች ውስጥ 21ኛን መርጦ ሙሉ በሙሉ ለምን ደመሰስኩ አለ?

21ኛ ጉና ክ/ጦር ከሃገራዊ ለውጡና ከሃገር ከሃዲዎች የመቀሌ መመሸግ ማግስት በኦሮሚያ ክልል የተፈጠረውን አለመረጋጋት ወደቀደመ ሰላሙ ለመመለስ ከጫካ ውጭ ሌላ የትግል አማራጭ የማያውቀውን የትህነግ ታናሽ ወንድም ኦነግ ሸኔን እግር በእግር ተከታትላ አፈር ድሜ ያበላችና ለአካባቢው ህዝብ እፎይታን የሰጠች ጀግና ክ/ጦር ናት ።

ዛሬም መንግስት ህግን ለማስከበርና የዘመናት የህዝቦችን ጥያቄ በዘለቄታዊነት ለመፍታት ተገዶ በገባበት ጦርነት ውስጥ ትውልድ የሚሻገር ገድል በራያ ግንባር ተሰልፋ በመስራት ላይ ትገኛለች፥ ከቆቦ እስከ አዲቀይህ ያለውን 160 ኪሎመትር የሚረዝም ፈታኝ የመሬት ገፅ በኢትዮጵያዊነት ፍቅር በተማረኩት ጅግና ልጆቿ ታጅባ የጠላትን መቃብር ያፋጠነች እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ጀግና ክ/ጦር ነች።

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address


Addis Ababa