Gohe Tv Broadcasting service
ጎህ የህዝብ ድምፅ🇪🇹
14/02/2024
"Our Strategic Partnership challenges us in more than one way.
If it is accepted, in terms of principles, that Africa must, for its peace, its security
and its sustainable development, count first and foremost on its own strengths,
its own genius, its own chain of solidarity, no one can deny the relevance, at this
stage of our evolution, of the need for mutually beneficial Partnerships with
others."
"የእኛ ስልታዊ አጋርነት ከአንድ በላይ በሆነ መንገድ ይፈትነናል።
ተቀባይነት ካገኘ፣ ከመሠረታዊ መርሆች አንፃር፣ አፍሪካ ለሰላሟ፣ ለደህንነቷ መረጋገጥ አለባት"
H.E. MOUSSA FAKI MAHAMAT
CHAIRPERSON OF THE AFRICAN UNION COMMISSION
FORTY FOURTH ORDINARY SESSION OF
THE EXECUTIVE COUNCIL
23/01/2024
አንጋፋው ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ከዚህ አለም በሞት ተለየ።
የስፖርት ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ የሀገራችንን ስፖርታዊ ክንውኖችን የሚያቀርብ እንዲሁም ከስፖርታዊ ክንዋኔዎች በተጨማሪ በጠቅላላ እውቀቱ እና መረጃ አያያዙ በርካታ እውቀቶችን ያስጨበጠ ጋዜጠኛ ነበር።
በተለያዩ የራዲዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራሞች ላይ ታሪኮችንና ወጎችን በማቅረብም በሚዲያው ላይ ከአርባ አመታት በላይ አገልግሏል።
አንጋፋው ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ “ ሊብሮ “ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ዛሬ ንጋት ላይ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
ጎህ ቴሌቪዠን ለመላው ቤተሰቦቹ ፣ ጓደኞቹ እና አድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል ።
22/12/2023
የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎቶቻቸውን በቴሌብር ለማቅረብ የሚስችል የዲጂታል ፋይናንስ ገበያ አገልግሎት ተጀመረ
*******************,
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮ ቴሌኮም የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎቶቻቸውን በቴሌብር ለደንበኞቻቸው ለማቅረብ የሚስችል የዲጂታል ፋይናንስ ገበያ እና የዲጂታል አክሲዮን ግዢና ሽያጭ አገልግሎቶችን በይፋ አስጀመረ።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ስለ አገልግሎቶቹ ማብራሪያ በሰጡበት በወቅት እንደገለፁት፤ አገልግሎቶቹ ሁሉም ባንኮች ኢንሹራንሶች እና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎታቸውን በቴሌ ብር መተግበሪያ በማስቀመጥ ለበርካታ ዜጎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያስችላል።
ይህም ብሔራዊ ባንክ በ2025 በአገር ደረጃ የፋይናን አግልግሎትን 70 በመቶ ለማድረስ ያስቀመጠዉን ግብ ለማሳት እና ዲጅታል ፋይናንሲንግን ለማሳደግ ይረዳል ብለዋል።
በተጨማሪም ሁለተኛው የአክሲዮን አገልግሎቶችን ለመግዛትና ለመሸጥ የሚያስችል ሲሆን፤ በዚህም ህጋዊ የሆኑ ባለአክሲዮኖች አገልግሎታቸውን በማቅረብ ብስልክ ቢቻ ለበርካታ ዜጎች ተደራሽ ይሆናሉ ሲሉ ገልፀዋል።
22/12/2023
የ18ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሜርሊግ ጨዋታ ትላንት ሲደረግ ክሪስታል ፓላስ ከብራይተን ያደረጉት ጨዋታ በአቻ ዉጤት ተጠናቋል፡፡ ዛሬም አንድ መርሃ ግብር አምስት ሰዓት ላይ ይደረጋል፡፡
ትላንት ምሽት አምስት ሰዓት ላይ ክሪስታል ፓላስ እና ብራይተን ያደረጉት የ18ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሜርሊግ ጨዋታ በአቻ ዉጤት ተጠናቋል፡፡
ክሪስታል ፓላስ ባሳለፍነዉ የዉድድር አመት ወደ ወራጅ ቀጠናዉ ላለመዉረድ ሲታገሉ መቆየተቻዉ ይታወሳል፡፡ በዘንድሮዉ የዉድድር አመትም የ76 አመቱን ሮይ ሀዲሰንን በዋና አሰልጣኝነት በድጋሜ ወደ ክለቡ በማምጣት ጥሩ የዉድድር አመትን ለማሳለፍ ቢሞክሩም እያሳለፉት ያለዉ፡የዉድድር አመት ግን እንዳሰቡት እየሆነላቸዉ አይደለም፡፡
በፕሪሜርሊጉ አስራ ስምንት ጨዋታቸዉን አድርገዉ አስራስምንት ነጥቦችን በመያዝ አስራአምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡
ትላንት ያደረጉትን ጨዋታም በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል፡፡ በተቃራኒዉ ያማረ እግር ኳስን የሚጫወቱት ብራይተኖች በምሽቱ የተሻለ የኳስ ቁጥጥር እና የጎል ማግባት ሙከራወችን ቢያደርጉም ክሪስታል ፓላስ ላይ ሙሉ ሶስት ነጠብ ይዘዉ መዉጣት አልቻሉም፡፡
በዚህ ጨዋታ ላይም ጆርዳን አዩ ለክሪስታል ፓላስ በመጀመሪያዉ የጭታ አጋማሽ ጎል ማስቆጠር ሲችል ደኒ ዉየሊቤክ ለብራይተን ከረፍት መልስ የአቻነት ጎል ማስቆጠር ችሏል፡፡
ዛሬም ምሽት አምስት ሰዓት ላይም አስቶን ቢላ ከሸፊልድ ዩናይትድ ጭታቸዉን በቪላ ፓርክ ያደርጋሉ፡፡
አስቶን ቪላወች በኡና ኤምሬ ስር ከወትሮዉ በተለየ ጥሩ የዉድድር አመትን እያሳለፉ ይገኛሉ፡፡ በተለይም በሜዳቸዉ የሚቀመሱ አይደለም፡፡ አርሰናል እና ማንችስተርሲቲ እንኳን በቪላ ፓርክ ሽንፈትን ቀምሰዉ ተመልሰዋል፡፡
አስቶን ቪላም ዛሬ ምሽት በፕሪሜርሊጉ መጨረሻ ደረጃ ላይ የተቀመጠዉን ሺፊልድ ዩናይትድን በሜደዉ የሚያስተናግድ ይሆናል፡፡ እናም የሚያሸንፍ ከሆነ ለጊዜዉም ቢሆን ፕሪሜርሊጉን በአንደኝነት የሚመሩ ይሆናል፡፡
በተቃራኒዉ ሸፊልድ ዩናይትዶች ከሜዳቸዉ ዉጭ እስካሁን ምንም ጨዋታ ማሸነፍ አልቻሉም ፡፡ እስካሁን ድረስ 17 ጨዋታወችን አድርገዉ ማሸነፍ የቻሉት ሁለት ጨዋታወችን ብቻ ነዉ፡፡
ታዲያ እነዚህ ሁለት ክለቦች ዛሬ ምሽት በቪላ ፓርክ ጨዋታቸዉን ያደርጋሉ፡፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Address
Addis Ababa