Kolfe Woreda 09 Communication
Govermen organizashion
26/05/2023
የኮልፌ ቀራኒዮ እና የፉሪ ክፍለ ከተማ አስተዳደሮች በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች ላይ በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል የፊርማ ስነ_ ስርአት ተካሔደ፡፡
ግንቦት 18ቀን 2015 ዓ.ም
ሁለቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደሮች በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች ማለትም በከተማ ጽዳት፤ በመሰረተ ልማት እና በመሰል ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት የሁለቱም ክ/ከተሞች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች፣ ዋና ስራ አስኪያጆች እና የሚመለከታቸው የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት የፊርማ ስነ ስርአት ተካሒዷል።
አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ በበኩላቸው ክፍለ ከተሞቹ አጎራባች በመሆናቸው የጋራ አገልግሎት መስጠት ስለሚገባ ሕዝቡን የሚያስተሳስር ስራ በልማት ፤በፅዳትና በሌሎች ስራዎች ላይ እንደ አስተዳደር ከእናንተ ጋር ተቀናጅትን እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል፡፡
የፉሪ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ወይንሸት ግዛው በተፈራረምነው ስምምነት መሰረት ያለንን አቅም በመጠቀም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ ያጋራ አላማችንን ማሳካት አለብን ለዚህም በቀጣይ ዕቅዶቻችን ውስጥ አካተን በልማትና በሌሎች ዘርፎች አብረን ተባብረን አንሰራለን ያሉ ሲሆን እናንተም ይህን ተረድታችሁ እዚህ በምጣታችሁ በክፍለ ከተማው ስም አመሰግናለሁ ብለዋል፡፡
አመራርነት ሁሉንም ህዝብ በእኩልበማገልገል ያሉትን ችግር በመካፈል መፍትሄ ለመስጠት ነው ያሉት አቶ አዱኛ ማሩ የሸገር ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ ሲሆኑ ዛሬ የጀመርነውን ስራ በከተማ ደረጃ ማስፋት አለብን እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማና ክፍለ ከተማዎቿ ጋር በአንድነት ለጋራ እድገት መስራት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ አስተዳደሮቹ በጋራ በሚሰሩባቸው ተግባራት ላይ ገለጻ በማድረግ የተወያዩ ሲሆን ከመድረኩም በተለያዩ የጋራ ጉዳዮች ላይ ህብረተሰቡን አስተባብረን በማሳተፍ በአንድነት ለማደግ እንሠራለን ሲሉም ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን ሰተዋል፡፡
25/05/2023
"በአብሮነት የህብረተሰቡን ጤና እንጠብቃለን"። በሚል መሪ ቃል የጤና ባለሙያዎች ውይይት እያደረጉ ነው።
ግንቦት 17/2015
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ /ቤት አዘጋጅነት የጤና ባለሙያዎች፣ የፋርማሲ ባለሙያዎች እንዲሁም የግሉ ዘርፍ የጤና ተቋማት በሀገራዊ ጉዳዮች በተጨማሪም በጤናው ዘርፍ የተገኙ ስኬቶችን የሚዳስስ ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ።
ተወያዩቹ በ5 ዓመት የለውጥ ጊዜያትን በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ ለውጦችን አስመልክቶ መወያየት ጀምረዋል።
ለውይይቱ መነሻ “በአብሮነት የህብረተሰብን ጤና እንጠብቃለን” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቧል።
25/05/2023
አንዲትም የኢባዱረህማን መስጂድ ህጋዊ ይዞታ እንደማይነካ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው አረጋገጡ።
የክፍለ ከተማው አስተዳደር በአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ስልምና ጉዳዮች ስራ አሰፈፃሚ ኮሚቴ ጋር በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር የነበረ በክፍለ ከተማው ወረዳ 05 የሚገኘው ኢባዱረህማን መስጂድ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ ስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ስራ አሰፈፃሚ ሰብሳቢ ኡስታዝ ሀሽም ሀምዛ
መስጂዱ እድሜ ጠገብና ታሪካዊ እንደሆነና በትላንቶናው እለት የተከናወነው ተግባር ተገቢ አለመሆኑን አስተዳደሩም መረጃውን አጥርቶ እርምጃ እንዲወስድ የጠየቁ ሲሆን ይዞታውን እንዲያስጠብቅ ጠይዋል።
አስተዳደሩ ተቀራርቦ በጉዳዮ ለይ በመወያየቱ ያመስግኑት ሰብሳቢው ከዚህ ቀደም እንደሚያደርጉት ሁሉ ተቀራርበው እደሚሰሩም አስታውቀዋል።
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨውን መረጃ አግባብነት የሌለው መሆኑን ገልፀው ክስተቱ በአስተዳዳሩ እውቅና እንደሌለውና ተቋማዊ አሰራርን ያልጠበቀ ሲሆን አስተዳዳሩ መረጃውን አጥርቶ ተጠያቂ እንደሚያደርግና አንዲትም የመስጂዱ ህጋዊ አካል እንደማይነካ አረጋግጠዋል።
አስተዳዳሩ ከመጂሊሱ ጋር በማህበራዊና የልማት ስራዎች ላይ ተቀራርቦ እየሰራ መሆንና ይህንንም እንደሚያስቀጥል አስታውቀዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለውም የተሳሳተ መረጃ በመያዝ ህዝበ ሙስሊሙ እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ማህበረሰቡም ትክክለኛ መረጃ ከአስተዳዳሩ እንዲወስዱ መልዕክት አስተላልፈዋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Telephone
Website
Address
Addis Ababa