Maysh Media.Com
የአራት ማዕዘናት የመረጃ ማዕከል
08/06/2026
4 ሎሚ ገበያ ይዘው የወጡት እናት ( እመትገሎ ኮበሺህ)!
"በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አራት ፍሬ ሎሚ ይዘው ለመሸጥ ገበያ ወጥተው በነበሩበት ምስላቸው የብዙዎችን ልብ የሰበሩትና ከፍተኛ መነጋገሪያ የሆኑት እናት እመት ገሎ ኮበሺህ፣ ሰይፉ ፋንታሁን አጊንቷቸዋል።
እመት ገሎ (Gelo Kebeshi) ይባላሉ። በአዲስ አበባ ከተማ ከ20 ዓመታት በላይ ኖረዋል። አማርኛ ቋንቋ ብዙም ስለማይችሉ የሚግባቡት በጉራጊኛ ነው።
ህይወታቸውን በጉሊት ንግድ እየደገፉ፣ በዚህ እድሜአቸው ዛሬም ድረስ በላስቲክ በተሰራ ጎጆ (መጠለያ) ውስጥ ነው የሚኖሩት።
እማማ ወደ ገበያ የወጡት 4 ፍሬ ሎሚ ብቻ ይዘው ነበር። የያዟት 4 ሎሚ ተሸጣላቸው፣ ለልጆቻቸውና ለልጅ ልጆቻቸው የሚሆን አንድ እንጀራ ገዝተው ለመግባት... የቤት ነገር ቢያስጨንቃቸው እንጂ በዚህ በደከመ እድሜአቸው ድጋፍ እንጂ ድካም አይገባቸውም ነበር።
እማማ ሰው እጅ ከመጠባበቅና ከመለመን ይልቅ፣ በወዛቸው ሰርተው ለመኖር የሚያሳዩት ተጋድሎ ለእኛ ለወጣቶቹ ትልቅ የሥራ ፍቅርና የጽናት ትምህርት ነው። ነገር ግን አቅማቸው የደከመ አረጋዊ እናት በመሆናቸው የሁላችንም ሰብአዊ ድጋፍ አሁን ያስፈልጋቸዋል።
የእማማን እንባ ማበስ የሁላችንም ድርሻ ነው።የባንክ አካውንት፦1000769117125 Gelo Kebeshi (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)"
24/05/2026
22 ዓመት ዛሬ ተሸነፈ
የፅናት ጉዞ በክብር ተሞሸረ
05/05/2026
ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ
በትግራይ ክልል ለሦስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የክልሉ ምክር ቤት በድጋሜ በመሰባሰብ ባካሄደው ጉባኤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ መረጠ። ምክር ቤቱ ወ/ሮ ኪሮስ ሓጎስን አፈ ጉባኤ፣ ወ/ሮ ምህረት በርሄን ደግሞ ምክትል አፈ ጉባኤ አድርጎ በመሾም ጉባኤውን አጠናቋል።
የክልሉ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት እና የፌዴራል መንግስት በጉዳዩ ላይ እስካሁን ያሉት ነገር የለም።(ማህበራዊ ድህረገጽ )
" "!
የሰሞኑ አነጋጋሪ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ የሚገርም ትወና ፣የሚገርም መልዕክት ።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the public figure
Telephone
Website
Address
Bole Road/Africa Avenue
Addis Ababa