MaBizplus
https://www.tiktok.com/@mabizplus?_r=1&_t=ZS-94lOqkY2SM0 The goal is to give simple, timely insights that help people stay informed through social media.
25/05/2026
የዕቃ አስተላላፊነት ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት ሆነ‼
MaBizplus
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ፣ የዕቃ አስተላላፊነት (Freight Forwarding) የኢንቨስትመንት ዘርፍን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ለማድረግ ወሰነ።
ቀደም ሲል በደንብ ቁጥር 474/2012 መሠረት ዘርፉ ለአገር ውስጥና ለውጭ ባለሀብቶች በቅንጅት ብቻ የተከለለ የነበረ ሲሆን፣ የውጭ ባለሀብቶች ድርሻም ከ49% እንዳይበልጥ ተገድቦ ቆይቷል። ይህ አሰራር በዘርፉ ላይ የሚፈለገውን የአዲስ ኢንቨስትመንት ፍሰት ገድቦት መቆየቱ ተገልጿል።
ይህ አዲሱ የቦርዱ ውሳኔ፡-
📌ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ዘመናዊ የሎጂስቲክስ አገልግሎት ለመስጠት፣
📌አገራዊ የሎጂስቲክስ ወጪን ለመቀነስ፣
የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማምጣት፣
📌 እንዲሁም የአገር ውስጥ ተዋናዮች አቅማቸውን አሳድገው ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Address
Sudan Street
Debra Markos