Abeni Home
መንግስት ኢትዮጵያ እንዴት
ለዜጎቿ የማትመች ሀገር መሆን እንዳለባት ከ IMF ጋር በትጋት እየሰራ ነው ተባለ!!
እውነትን እና ሂወትን ከኖረ ሰዉ ምክር ደስ ሲል።
25/05/2026
በተለይ በወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የሚፈጸሙ ያልተገቡ አሠራሮችንና «ውንብድናዎችን» በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ ይፋ በማድረግና በማጋለጥ የሚታወቀው ወጣት አቤል አቡና፣ ሰሞኑን በሰጠው ጠንከር ያለ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ትችት ሳቢያ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መታሰሩ ተሰምቷል። ወጣቱ በቁጥጥር ሥር የዋለው፣ ታዋቂው ዓለም አቀፍ የአጫጭር ቪዲዮ ዜና አቅራቢ ዲላን ፔጅ አዲስ አበባ መግባቱንና የብልፅግና መንግሥትም ታዋቂ ሰዎችን በመጠቀም «ሠራኋቸው» የሚላቸውን የኮሪደርና የልማት ሥራዎች ለዓለም እያሳየ በሚገኝበት የወቅቱ ትኩስ አጀንዳ ላይ የሰነዘረውን የሰላ ድምፅ ተከትሎ ነው።
አቤል አቡና በቁጥጥር ሥር ከመዋሉ በፊት ባስተላለፈው መልእክት፣ የመንግሥትን የወቅቱን እንግዶችን የመቀበልና የከተማ ገጽታ ግንባታ ሒደት በጥልቀት የተቸተ ሲሆን፤ የወቅቱን የኢትዮጵያን ሁኔታ ሲገልጽም፦ «ኢትዮጵያ ሳሎኗን ብቻ አፅድታ፤ የጓዳ ቆሻሻዋን ደብቃ እንግዶችን የምትቀበል ሰነፍ ሴትን ትመስለኛለች» የሚል ይፋዊ አስተያየት ሰጥቷል። ይህ የወጣቱ ንግግር በከተማዋ ላይ የሚታዩትን ውጫዊ ውበቶችና ዘመናዊ ግንባታዎች እያደነቁ፣ በጓዳ በኩል ያሉትን በርካታ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የሕዝቡን የኑሮ እውነታዎች ወደ ጎን መሸፈንን የሚተች በመሆኑ በመንግሥት ሰዎች ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል ተብሏል።
የዚህ ወጣት መታሰር በማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ሰፊ መነጋገሪያና ቅሬታን የፈጠረ ሲሆን፣ መንግሥት የዜጎችን የመናገርና የመተቸት መብት ከማክበር ይልቅ እንዲህ ያሉ የሰላ ሂሶችን በኃይል ለማፈን እየሞከረ ነው የሚሉ ትችቶችንም እያገነፈለ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት ወጣቱ በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና ይፋዊ የክስ መመሥረቻ እንደቀረበበት ከመንግሥት ወገን የተሰጠ ዝርዝር መረጃ የለም።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the public figure
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
1332