Armauer Hansen Research Institute
The Armauer Hansen Research Institute (AHRI) was founded in 1970.
19/06/2026
በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት እና በአህሪ መካከል የኮሙዩኒኬሽን ስራዎች የልምድ ልውውጥ ተካሔደ
የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የኮሚኒኬሽን የስራ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች የአመራርና የሙያ አቅማቸውን ለማሳደግ እንዲሁም የተቋማትን የመረጃ ፍሰትና ግንኙነት ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግ በአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (አህሪ) የስራ ጉብኝትና የልምድ ልውውጥ አካሄዱ።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ በልምድ ልውውጡ መርሀ ግብር ተገኝተው እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የተቋማቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን በቀጣይም ከኮልፌ ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ጋር በጋራ ተቀናጅተው በመስራት የማህበረሰቡን የመረጃ ተደራሽነት ለማስፋት በትኩረት አንደሚሰራ ተናግርዋል ።
የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ምርምር ሀይሌ በበኩላቸው የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (አህሪ) በርካታ የምርምር ውጤቶች ውጤታማ በሆነ መንገድ በማምረት ለሀገር የሚተርፍ ስራ እያከናወነ መሆኑን ገልፀው በቀጣይም በጋራ ልምድ በመውሰድና ተባብሮ በመስራት ተቋሙ ለማህበረሰቡ ለማስተዋወቅ ጠንካራ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል።
ይህ የልምድ ልውውጥ የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ስራዎችን በቴክኖሎጂ በመደገፍ፣ ወቅታዊና ተዓማኒ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራትን እና የጋራ የእርስ በእርስ ግንኙነትን ለማጠያከርና በቀጣይ በጋራ ለመስራት ታሳቢ ያደረገ ነው።
በጉብኝቱና በልምድ ልውውጡ ወቅት የክፍለ ከተማው የኮሚኒኬሽን አመራርች፣ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች በአህሪ እየተከናወኑ ያሉ የዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀም፣ የኮንቴንት (ይዘት) ዝግጅት፣ የሚዲያ ክትትልና ትንተና እንዲሁም የስራ አካባቢ አደረጃጀቶችን በቅርበት ተመልክተዋል። በተለይም ውስብስብ የሆኑ የምርምርና የሳይንስ መረጃዎችን ለሰፊው ህብረተሰብ በተሻለ ጥራት፣ ቀላልና ሳቢ በሆነ ይዘት ማስተዋወቅ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በመጨረሻም የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የኮሚኒኬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች ከዚህ ጉብኝት ያገኟቸውን ጠቃሚ አሰራሮች ወደ ስራ በመቀየር፣ በቀጣይም ከተቋሙ ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/106861043/admin/dashboard/
Website:
https://ahri.gov.et/
Facebook: https://web.facebook.com/AHRIGovEt/?_rdc=1&_rdr #
Youtube: https://www.youtube.com/
Telegram:
https://t.me/ahriethiopia
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the school
Website
Address
Addis Ababa
Opening Hours
| Monday | 08:00 - 17:00 |
| Tuesday | 08:00 - 17:00 |
| Wednesday | 08:00 - 17:00 |
| Thursday | 08:00 - 17:00 |
| Friday | 08:00 - 17:00 |