Samuel demise

Samuel demise

Share

Daily thoughts and random moments 🤠

Ethiopia 🇪🇹 🇪🇹 🇪🇹

Photos from Samuel demise's post 05/05/2026

#ጽዮናዊነት

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትም ፍልስጤምን ለሁለት ተከፍላ የአይሁዶች እና የአረቦች የተናጠል አገራት እንዲመሠረቱ ሃሳብ አቀረበ። በአውሮፓውያኑ 1948 እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ ውስጥ በአገርነት መመሥረቷ ታወጀ።
በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ከቀያቸው እና ከቤታቸው ተፈናቅለዋል።

ከዚያም በኋላ እ.ኤ.አ በ1967 የተደረገውን የስድስቱን ቀን ጦርነት ተከትሎ የፍልስጤም ግዛቶች የሚባሉትን ዌስት ባንክ እና ምስራቅ እየሩሳሌምን እስራኤል በኃይል ተቆጣጥራ ትገኛለች። ባለፉት አምሳ አራት ዓመታትም በእነዚህ ግዛቶች የአይሁዶች የሰፈራ መንደሮችን አቋቁማለች። 700 ሺህ የሚቆጠሩ አይሁዳውያን በእነዚህ ሰፈራዎች ይኖራሉ።

የተባበሩት መንግሥታትን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት እስራኤል በቁጥጥሯ ስር ባሉ ግዛቶች የሰፈራ መንደሮችን ማቋቋሟ ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጻረር እና ሕገወጥ ነው ሲሉ ይጠራሉ። የእስራኤል መንግሥት ምስረታ በፍልስጤም የሚኖሩ አረቦችን መብት የገፈፈ መሆኑን በመጥቀስ ፍልስጤማውያን እንዲሁም ሌሎች አረቦች ይቃወሙታል::

የጽዮናዊነትን እንቅስቃሴ የሚያንቀሳቅሱ አካላት እስራኤል እንደ አይሁድ ግዛትነቷ ጥበቃ ሊደረግላት እንዲሁም ልትስፋፋ ይገባል ብለው ያምናሉ። አንዳንድ ጽዮናውያን እስራኤል ካላት ግዛት በተጨማሪ ሌሎች ግዛቶችንም የመቆጣጠር መብት አላት ብለው የሚከራከሩ ሲሆን፣ ሌሎች በዚህ ሃሳብ አይስማሙም። አብዛኛው አይሁዳውያን ጽዮናውያን ቢሆኑም፣ ጥቂቶች በፖለቲካዊ እና በሃይማኖታዊ ምክንያቶች ጽዮን ሃሳብን ይቃወማሉ። አይሁዳዊ ያልሆኑ ሰዎች ጽዮናዊነትንም መደገፍ ይችላሉ።

ጽዮናዊነት በአውሮፓ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የተጀመረ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ነው። ፍልስጤም በምትባለውም ምድር የአይሁድ አገርን መመሥረት ዋነኛ ግቡ ነው። ይህ እንቅስቃሴ የአይሁዳውያን የጥንት ርስት ናት የሚሏትን የአይሁዳውያን አገር የሆነች እስራኤል ፍልስጤም ተብሎ በሚታወቀው መሬት የመመሥረት ፍላጎት የነበረ ነው።

Photos from Samuel demise's post 05/05/2026

ኢትዮጵያ ከ1928 ዓ.ም. ከሚያዝያ 27 ቀን (አዲስ አበባ በፋሽስት ኢጣሊያ የተያዘችበት) እስከ 1933 ሚያዝያ 27 ቀን (አዲስ አበባ በድል የተያዘችበት) ድረስ የጠላት ኰቴ በመስኮቿ ላይ ቢዛወርም ገዢነቱን አላወቀችለትም፡፡ ጫካው ሁሉ የዳርቻ ወሰኗ ስለሆነላትና ሜዳውም ቢሆን እሾሀማ ብቻ ሆኖ ስለአስቸገረው ምን ያህል ጭንቀት እንዳደረሰበት አምስት ዓመት ያልሞላው የሥቃይ ዘመን ምስክር ነው

Want your place of worship to be the top-listed Place Of Worship in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address


Addis Ababa