Insurance Fund Administration Agency

Insurance Fund Administration Agency

Share

The FDRE Proclamation No. 799/2013 introduced Vehicle Insurance Against Third Party Risks. This is t

Photos from Insurance Fund Administration Agency's post 13/06/2022

በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚወጡ እስትራቴጂዎች፣ ፖሊሲዎች፣ ህጎች እና ደንቦች የተሸከርካሪ አደጋን ለመቀነስ የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወጡ ተገለፀ፡፡
የመንገድ ደህንነትና የመድን ፈንድ አገልግሎት በደንብ ቁጥር 493/2014 በተሰጠውን ስልጣንና ተግባር እና አለማቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ህጎች ላይ በካፒታል ሆቴል በ6/10/20141 ዓ.ም ከባለድርሻ አካላት ጋር ወርክሾፕ አካሂዶል፡፡
በዕለቱን ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመንገድ ደህንነትና የመድን ፈንድ አገልግሎት የኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ አዲል አብዱላሂ አንደገለፁት አገልግሎቱ የተሰጠውን ስልጣንና ተግባር የማስተዋወቅ፣ የመንገድ ትራፊክ ደህንንነት ህጎችን የማስፈፀም እና በአለም አቀፍ ደረጃ የወጡና ሀገራችን የተስማማችበትን የመንገድ ደህንነትና የመድን ፈንድን የሚመለከቱ ስምምነቶች መተግበርና አፈፃፀማቸውን መከታታል ለመቤቱ ከተሰጡት ስልጣን ውስጥ እንደሚጠቀስ በንግግራቸው ገልፀዋል፡፡
በወርክሾፑ ላይ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ ማቋቋሚያ በድንብ ቁጥር 493/2014 የተሰጡትን ስልጣንና ተግባራት በአቶ ዮናስ በለጠ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን ከዚህም ጋር በተያያዘ የብሉምበርግ ኢንሼቲቭ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ዮሃንስ ለገሰ የመንገድ ደህንነት አለማቀፍ ተሞክሮዎችን በህግ አተገባበር ላይ ያሉ ክፍተቶችን እና የአደጋ መንስኤ አቅርበዋል፡፡ እንደ ሃገርም በዘርፉ በተለያያ ጊዜ የመንገድ ደህንነት የህግ መእቀፎችን ለማሻሻል በወጣው የትራፊክ ደንብ ቁጥር 208/2011 ላይ ያሉትን የትርጉም ክፍተቶችን በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተደርበታል፡፡
በመጨረሻም በቀረበው ሰነድ ላይ ከተሳተፊዎች በተነሱ ጥያቄዎች ውይይት ተደርጓል፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ የአለም አቀፍ የህግ ማስከበር ሰኬትና ተሞክሮዎች ቀርበው በሃገር ደረጃ በየጊዜው ለሚደርሱ አደጋዎች የመጀመሪያው ክፍተት ህግን ማስከበር ላይ እንደሆነና በዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶች ላይ ትኩርት እንዲሰጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለመንገድ ትራፊክ አደጋ መቀነስ የድሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ ተደርጎ የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡

የመንገድ ደህንነት ማስጠበቅ የቁጥጥር ዘመቻ 17/05/2022

የመንገድ ደህንነት ማስጠበቅ የቁጥጥር ዘመቻ የመንገድ ደህንነት ማስጠበቅ የቁጥጥር ዘመቻ

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Address


Kazanchis Elily International Hotel Building 2 (3rd & 4th Floor)
Addis Ababa
1288