Addis Ababa University
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
06/05/2026
ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የጥናት፣ የምርምር እና የሥራ አውደ ርዕይ ሳምንት ተከፈተ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 7ኛው የምርምርና የሥራ አውደርዕይ ሳምንት "Advancing Education through Research Digitalization Innovation and Industry partnerships" በሚል መሪ ቃል ዛሬ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ የመክፈቻ መርሀ ግብር ተከፍቷል።
የዘንድሮው የምርምር ሳምንት በዩንቨርሲቲው እየተተገበረ ከሚገኘው የ5 አመቱ ስትራቴጂክ እቅድ ጋር የተጣጣመ አላማ ያለው መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ገልጸዋል።
አውደ ርዕዩ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት የተሰጠውን የዲጂታላይዜሽን እንቅስቃሴ ለትምህርት ስርዓት፣ ለፈጠራ እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ማስተሳሰር ላይ ያተኮረ የምርምር ሳምንት መሆኑን የዘንድሮው የምርምር ሳምንት ዋና አዘጋጅ የሆነው የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ኤክስኩቲቭ ዲን የቆየአለም ደሴ (ዶ/ር) ጠቁመዋል።
በዕለቱ ከመክፈቻው መርሀ ግብር ጎን ለጎን የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና የዪኒቨርሲቲውን ምሁራን ያካተተ በሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል።
በቀጣይ ቀናት በሚኖሩ መርሃ-ግብሮች የተለያዩ ኮሌጆች ምሁራን የተሰሩ የምርምር ውጤቶች የሚቀርቡ ሲሆን የላቀ ግኝት ላገኙ እውቅና የመስጠት መርሃ ግብርም የሚካሄድ ይሆናል።
24/04/2026
የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከልን (China-Africa Research Center) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈረመ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ትብብር የሚቋቋመው ይህ ማዕከል በቻይና እና በአፍሪካ መካከል ያለውን አካዳሚያዊ ትብብር በማጠናከር፣ የባህል ልውውጥን ለማሳደግ እና የጋራ የምርምር ሥራዎችን ለማከናወን ያለመ ነው።
የማዕከሉ መቋቋም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ለዓመታት የዘለቀ ጠንካራ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ውጤት መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ወቅት ገልጸዋል።
የቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ፕሬዝዳንት ክቡር ዬ ሃይሊንግ (Ye Hailing) በበኩላቸው ማዕከሉ በቻይና መንግሥት ከሚደገፉት 25 የቻይና-አፍሪካ ምርምር ማዕከላት መካከል እንዱ መሆኑን ጠቅሰው በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂካዊ አጋርነትም ይበልጥ እንደሚያጠናክረውም ጠቁመዋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the school
Telephone
Address
Addis Ababa University
Addis Ababa
1176