Addis Zeybe

Addis Zeybe

Share

Get updated with the latest Ethiopian news and stories from more than 13 towns across the nation.

25/09/2023

#ማሳሰቢያ
በአዲስ አበባ ከተማ ከዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ የሞተር ሳይክል እንዲሁም የባጃጅ እንቅስቃሴዎች በሙሉ ይቆማሉ

መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፤ አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከዛሬ ማታ 12 ሰዓት ጀምሮ የሞተር ብስክሌተኞች፣ ባለ አራት እና ባለሶስት እግር ባጃጅ አሽከርካሪዎች በሙሉ ከእንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

ቢሮው እንዳስታወቀው ከዛሬ መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ማክሰኞ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ድረስ ማለትም ለ15 ቀናት ማሽከርከር አይችሉም።

ክልከላው የፀጥታ እና የትራፊክ ቁጥጥር የሚሰሩ አካላትን አያካትትም ያለው የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ቢሮው እየገለፀ፤ ይህንን መልእክት በሚተላለፉ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ሲል ቢሮው አሳስቧል።

20/09/2023

+ መስከረም 9/2016
በጤና፣ ትምህርትና የምግብ ዋስትና ላይ አደጋ የሆነው የአማራ ክልል ግጭት እና ሌሎች የዕለቱ መረጃዎች

19/09/2023

📻 የጦር እና በሰብዓዊነት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች እንዳይመረመሩ የኢትዮጵያ መንግስት ጫና እያደረገ መሆኑን ተመድ አስታወቀ

✍ የኢትዮጵያ የሽግግር ጊዜ ፍትህ ሂደት በመንግስት ጫና የተጠለፈ እና ተጎጂዎች “ተስፋ የቆረጡበት” መሆኑን የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ያስታወቀ ሲሆን የኮሚሽኑ የስልጣን ዘመን እንዲራዘም ምክረ ሀሳብ ቀርቧል

✍ ከ500 የሚበልጡ የዓይን እማኞች ቃለ መጠይቅ የተደረጉበት ሪፖርት በትላንትናው እለት የቀረበ ሲሆን “የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ ህገ መንግስትም ጭምር ግዴታው የሆነውን የዜጎቹን ደህንነትና ሰብዓዊ መብት መጠበቅ እንደተሳነው” ጠቁሟል።

✍ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ሁኔታዎች ሳቢያ ታኅሣሥ 8 ቀን 2013 ዓ.ም. የተመሰረተው የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽኑ ለአንድ አመት እንዲቆይና እንደ አስፈላጊነቱ እንዲራዘም ተወስኖ ነበር የተቋቋመው።

✍ የፌደራል መንግስት ከህወሓት ጋር ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. በጀመሩት ጦርነት ምክንያት የተቋቋመው ኮሚሽን ሰብሳቢ ሞሀመድ ቻንዴ እንደገለፁት፤ በፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ግጭቶችን በዘላቂነት ማስቆምም ሆነ ሰላም መፍጠር አልቻለም ብለው በታጣቂ ኃይሎች የሚፈፀሙ ወንጀሎች መበራከታቸውን ጠቁመዋል።

ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ https://am.addiszeybe.com/featured/addis-ababa/the-united-nations-has-announced-that-the-ethiopian-government-is-putting-pressure-on-war-crimes-and-crimes-against-humanity-to-be-investigated

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Addis Zeybe

Addis Zeybe is a digital news media outlet dedicated to reporting news related to Ethiopia in an independent and fair manner. Our main focus areas are issues related to urbanization and professionalism in different parts of Ethiopia. Previously operating under the name Gobena Street, Addis Zeybe is committed to creating timely and accurate digital news contents via its website and other social media outlets. Join us now to get all news related to Ethiopia. We are committed to everything Ethiopia!

Website - http://addiszeybe.com/
Twitter - https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook - https://www.facebook.com/Addiszeybe/
Instagram - https://www.instagram.com/addiszeybe/
Telegram - https://t.me/AddisZeybe
YouTube - https://www.youtube.com/channel/UC_GAiujz7Otwc3X4-GrhLZg
Linkedin - https://www.linkedin.com/company/addiszeybe/

Telephone

Address


Gabon Street
Addis Ababa
0000