Bisrat Promotion
በአካል ጉዳተኝነት እና ጉዳተኞች ላይ የሚሰራ…እያዝናናን እ? A Multimedia Initiative Focused on Raising Disability Awareness!
29/08/2024
ነፍስ ይማር🙏💔
ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ አረፉ 😭😭
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ማረፋቸውን አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከደቂቃዎች በፊት አስታውቋል።
ፕሮፈሰር እንድሪያስ እሸቴ አካል ጉዳተኛ ለሆኑ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በስራ ዘመናቸው ከፍተኛ አገልግሎት የሰጡ ግለሰብ ናቸው
28/07/2024
አቢሲኒያ ሽልማት🏅
👏👏
"ትጉኋንን እንሸልማለን" በሚለው መርሀ ግብር
በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል
የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ ሴቶች ብሄራዊ ማህበር ዛሬ 21/11/2016 ዓ.ም ተሸልማለች።
እንኳን ደስ አላችሁ 👏🤟🥇
24/07/2024
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ ምክንያት የዜጎቻችን ህይወት በመቀጠፉ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እገልፃለሁ።
በተከሰተው ድንገተኛ አደጋ ሳቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖችና ለተጎጂ ቤተሰቦች ወዳጅ ወመዶች ሁሉ መፅናናትን እንመኛለን ።
20/03/2024
የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ከኢትዮ ቴሌ ኮም ጋር በመተባበር 500 ለሚሆኑ የተለያየ አካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች ድጋፍ አደረገ።
ደጋፍ ለተደረገላቸው ተማሪዎች በአካል ድጋፍ እና የቴክኖሎጂ መርጃ ቁሳቁስ እጦት ምክንያት ትምህርታቸውን እንዳያቆርጡ የዊልቸር፣ የክራንች፣ የነጭ በትር እና የጆሮ ማዳመጫ ናቸው ።
ድጋፉ በአዲስ አበባ ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች የተከናወነ ሲሆን በሌሎች ክልሎችም የሚቀጥል መሆኑን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ ተናገረዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ኮሚንኬሽን ኦፊሰር መሳይ ወብሸት ኩባንያው ያደረገው ድጋፍ ማህበራዊ ሀላፊነቱን ለመወጣት ያደረገው መሆኑን ተናግረዋል።
26/02/2024
ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ‹‹ለተሻለ ነገ እናንብብ ››የሁለተኛ ቀን መራጭ ደራሲ ዘነበ ወላ ነው፡፡ደራሲው የማንበብ ልምዱን እንዲህ አጋርቷል፡፡
‹‹እኔ 24 ሰዓታት ስራዬ ብዬ የማነብበት ጊዜ አለ፤ ጠዋት ከእንቅልፌ ከመነሳቴ በፊት አነባበለሁ፡፡ ስተኛም እንደዛው፤ በቦርሳዬ ውስጥ የማነበውን ነገር ይዤ ነው የምንቀሳቀሰው፡፡ 24 ሰዓታት ማንንም በስልክ ሳላናግር ልቆይ፤ ሁለት እና ሶስት ቀን አልፎም ሳምንት ከቤት ሳልወጣ ላነብ እችላለሁ፡፡ ››
ደራሲ ዘነበ ወላ ህዝቡ ቢያነባቸው ደስ የሚለኝ የምንግዜም ምርጥ መፅሃፍት ምርጫዎቼ በማለት የሚከተሉትን ዘርዝሯል፡፡
1 ፍቅር እስከ መቃብር፡- ሀዲስ አለማየሁ
2 ከአድማስ ባሻገር ፡- በዓሉ ግርማ
3 የታንጉት ምሥጢር፡- ብርሃኑ ዘርይሁን
እንደተወዳጁ ደራሲ ዘነበ የማንበብ ትልቁ ጥቅሙ አንብበህ የራስህን ሃሳብ ማሰብ እንድትችል ማድረጉ ነው፡፡ ስታነብ ደስታን ትገበያለህ፤ ቋንቋህ ያድጋል በሃሳብ ትመጥቃለህ፤ በአንድ ጉዳይ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ከማሰብ ትወጣለህ፤ እውነትህን በእራስህ እምነት ልክ ብቻ ከማየት መላቀቅ የምትችለው ስታነብ ነው ይላል፡፡
እርስዎም የራስዎን ምርጥ 3 መፅህፋት መርጠው ያጋሩ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
27526