EECMY Referal Congregation Hawassa
ለወንጌል የምትኖር ቤተ-ክርስቲያን!!
24/05/2026
የ"ጉበኛ ለትውልድ" የጸሎት መርሀግብር ለሀገር ሰላምና ለምርጫ ስኬት ተጠናቀቀ::
"ጉበኛ ለትውልድ ዓለም አቀፍ አገልግሎት" በኢትዮጵያ ሰላም፣ ለመንፈሳዊ መነቃቃት እና ለምርጫው ስኬታማነት ሲያካሂድ የቆየውን የ5 ቀናት ልዩ የጾምናጸሎት ኮንፈረንስ በድምቀት አጠናቀቀ።
በኮንፈረንሱም
በግንቦት ወር ለሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ስኬት እና የሀገሪቱን ሰላም በጸሎት አደራ ብለዋል።
በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የመጨረሻው ዘመን ሪቫይቫል እንዲቀጣጠልና አማኞች ክርስቶስን እንዲመስሉ ጥሪ ቀርቧል ::
በሀገራችን የሚታዩትን የሙስና፣ የጥላቻና የደም መፋሰስ ችግሮች እንዲያቆሙ ምልጃ ተደርጓል።
ለወጣቱ ትውልድ፡ 70 በመቶው የኢትዮጵያ ወጣት በሥነ-ምግባር የታነጸ፣ በሳይንስና በፈጠራ የዳበረ አእምሮ ያለው ትውልድ እንዲሆን ተጸልየዋል።
ለኢትዮጵያውያን፡ በደቡብ አፍሪካ ለሚገኙ ወገኖቻችን ጥበቃና ሰላም እንዲሁም ለእስራኤል ሰላም ልዩ ምልጃ ቀርቧል።
የአገልግሎቱ ባለራዕይ አገልጋይ ነገደ ወልደ ሰንበት፣ አማኞች በጸሎትና በአንድነት ለሀገር ሰላምና ለንጹህ ሕይወት እንዲተጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ
ዘገባው ዳንኤል አንተነህ ነው
21/05/2026
ደሙ ነዉ ዋስትናዬ. አዲስ መዝሙር የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ ሪፈራል ማህበር ምዕመናን ሀዋሳ ፋሬስ መዘምራን 2017 ዓ ም Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
19/05/2026
በመጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ቢሮ የወጣ ታሪካዊ ውሳኔ
መካነ ኢየሱስ ራሳቸውን "ሐዋርያት" እና "ነቢያት" ብለው የሚጠሩትን ጨምሮ የሌሎች ቤተ እምነት አገልጋዮች በመድረኬ ላይ እንዲጋበዙም ሆነ አገልጋዮቼ በእነርሱ መድረክ ላይ እንዲቆሙ አልፈቅድም ብላለች። ይህንን በሚያደርጉ እና ውሳኔዋን በሚተላለፉ ቄሶችና ወንጌላውያን ላይ ቅስናቸውን እስከ መግሰስ እና ከወንጌላዊነት መደብ እስከ ማንሳት የሚደርስ የማያዳግም እርምጃ እንደምትወሰድ ጠንከር ያለ መልእክት አስተላልፋለች።
"ብልጥ ልጅ የተሰጠውን ይዞ ለቀረው ያለቅሳል" እንዲሉ፣ ስለዚህ ታላቅና ታሪካዊ ውሳኔ መሪዎቻችንን እያመሰገንን፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ከካውንስል እና ከሉተራን ዎርልድ ፌዴሬሽን ሕብረት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለቃ መውጣቷን እስክናረጋግጥ ድረስ ቃለ እግዚአብሔርን መሠረት ያደረገ ሙግታችን የሚቀጥል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።
18/05/2026
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ሪፈራል ማህበር ምዕመናን
================================
ግንቦት 09/09/2018 ዓ.ም ሀዋሳ
መልዕክት አቅራቢ: ፍሬው ሀ/ማሪያም
የመነሻ ጥቀስ: መዝሙር ዳዊት 25_3
ርዕሰ: ተስፋችንን አጥብቀን እንያዝ ።
-----------------------------
ተስፋችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
1. ተስፋ የሰጠን እርሱ የታመነ ነውና ተስፋችን የሆነውን ኢየሱስን በመከራ ጊዜም ይሁን በደስታ ጊዜ እርሱን ማሰብ ያስፈልጋል።
2. በእግዚአብሔር ላይ ተስፋ ያደረገ ሰው ምንም ዓይነት ችግር በሚደርስበት ጊዜ በችግርና በመከራ ውስጥ ሆነው ተስፋው ኢየሱስ እንደሆነ ያስባል አይናወጥም።
1. እግዚአብሔርን ተስፋ ያደረገ ሰው ተስፋውን በችግር፣በመከራ እንድሁም በስኬት አይለካም። በሞት ጥላ ውስጥ ሆነው የማይሞት ተስፋ ይጠበቃል።
2. ተስፋን አጥብቆ የያዘ ሰው ለቤተክርስቲያን ፣ ለቤተሰበ፣ ለራሱ እና ለሀገር እንደ አብርሃም በረከት ይሆናል። ዘፍ 12፥1
ስለዚህ ከሁኔታው፣ ከችግር፣ከመከራ፣ከስኬት እና ካለን ነገር በላይ እግዚአብሔርን ተስፋ ማድረግ አያሳፍርም። ተስፋችን በእምነት እና በፍቅር በትዕግሥትም እንያዝ።
“አንተን ተስፋ የሚያደርጉ አያፍሩም፤ በከንቱ የሚገበዙ ያፍራሉ።”
መዝሙር 25፥3
ኢየሱስ ጌታ ነው!!
👇
የማህበር ምዕመናን ዲጂታል የወንጌል አገልግሎት ዘርፍ
ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ከታች ያለው Page Follow በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
https://tr.ee/VcHXkRfRGI
Facebook
https://www.facebook.com/share/1BX2xBEgrx/
YouTube
https://www.youtube.com/
Telegram
https://t.me/EECMYR70
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the place of worship
Telephone
Website
Address
Referal Mekanyesus
Awassa
REFERALMEKANYESUS