Gech Gm page

Gech Gm page

Share

Digital crater

01/10/2025

‎ከመስከረም 21 እሰከ 30/2018 ዓ.ም የሚኖረው የአየር ሁኔታ አዝማሚያ

‎በመጪዎቹ አሥር ቀናት አሁን ከሚታዩትና በቀጣይነትም ከተተነበዩት የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በደቡብ፣ በምስራቅ፣ በደቡብ ምዕራብና በምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ ገጽታ ይኖራቸዋል፡፡

‎በመሆኑም በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የጉጂ፣ ምስራቅ ጉጂ፣ ምስራቅ ቦረና ዞኖች፤ የሲዳማ ክልል ዞኖች፤ የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ዞኖች እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዞኖች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

‎በተጨማሪም ቀደም ብሎ የክረምት ወቅት ዝናብ ሲያገኙ የነበሩ የምዕራብ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ እንዲሁም ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ቀጣይነት ይኖረዋል፡፡

‎በተጨማሪም በፀኃይ ሀይል ታግዞ ከሚጠናከሩ የደመና ክምችቶች ላይ በመነሳት በምዕራብ፣ በመካከለኛዉ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናት በ24 ሰዓት ውስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው የብሔራዊ ሜቲዎሮሎጂ መረጃ ይጠቁማል።

‎ #ከማምረትበላይ


‎በፌስቡክ https://www.facebook.com/southwestethiopiaagriculturebureau/ ያገኙናል።

Photos from Ministry of Agriculture - Ethiopia's post 08/07/2025
Want your practice to be the top-listed Law Practice in Bonga?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Address


Bonga