Harar Polytechnic College
Harar Polytechnic College
29/12/2025
በሐረሪ ክልል የ 2018 ዓ.ም ሁለተኛ ዙር ክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ መርሃግብር ለክልሉ ለሥራ ኣጥ ነዋሪዎች በገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠና ላይ ለሰልጣኞች ኦረንቴሸን ተሰጥቷል።
በሐረሪ ክልል የወጣቶች ክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ የገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናዎች ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቀው በሐረር ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ የሰልጣኞችን የምዝገባ መርሃግብር ተከትሎ በዛሬው ዕለት ኦረንቴሽን ተሰጥቷል።
በኦረንቴሽን መድረኩ ላይ
የሐረሪ ክልል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ኢማን መሐመድ፧ አቶ ኡስማኢል ዩሱፍ የኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ኃላፊ ፣ አቶ አሰፋ ቶልቻ የሐረር ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን እና የሀረሪ የማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ተወካዮች የኦረንቴሽን መድረኩን ላይ በመገኘት ለሠልጣኞች የእንኳን ደህና መጣቹ መልዕክት እና በሥልጠናው ዙሪየ ለሠልጣኞቹ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ታህሳስ 20/2018ዓ.ም
02/12/2025
በሐረሪ ክልል ለሐረር ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለብልጽግና ፓርቲ አባላት "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ሥልጠናው የአባላቱን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነቡ ልዩ ልዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚቀርቡበት ሲሆን ለተከታታይ 2 ቀናት በሚኖረው ቆይታ፥በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣የገጠርና የመዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ፣የኢንዱስትሪ ዘርፍ ፣የከተማ ልማት እንዲሁም የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ በሚል ርዕሶች ስልጠናው የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።በውይይት መድረኩ ላይ
የሐረር ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ አሰፋ ቶልቻ በሥልጠናው ዙሪየ ለአባላቱ በቀረበው ፅሁፍ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ህዳር 23 /2018ዓ.ም
21/11/2025
የሐረር ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አለም አቀፍ የኢንተርፕሬነር ሺፕ ሳምንት በተለያዩ ኩነቶች አከበረ።
በፕሮግራሙ ላይ የሐረር ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ አሰፋ ቶልቻ፣የቴ/ሙ/ት/ሥ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ወ/ሮ ኢማን መሐመድ፣ የኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማኢል ዩሱፍ ፣የልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር አቶ በዳሳ ገመዳ ፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፣የኮሌጁ አሠልጣኝ መምህራን፣አስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም ሠልጣኞች በተገኙበት በተለያዩ ኩነቶች ተከበረ።
21/10/2025
የምን ባለሙያ መሆኑ ይፈልጋሉ?
የቴክኖሎጂ 🖥️፣ የውበት 💄፣ የአውቶሞቲቭ 🚗፣ የፈርኒቸር 🪑፣ የሆቴልና ቱሪዝም 🏨🍔🍕፣ የኮንስትራክሽን 🏗️፣ የፋሽን ዲዛይን 👗✂️ የኤሌክትሪካ 🔌🪛፧የመኑፋክቸሪንግ⛓⛓💥🛡፧የሰርቬይ እና ድራፍቲንግ📝🔭 ፧የአካውንቲንግ 💰💰💰
ፍላጎትዎን እውን ያደርጉ ዘንድ የሐረር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ለምዝገባ በመደበኛ፧በምሽት እና ቅዳሜ እና እሁድ እርስዎን ተቀብሎ ለማሠልጠን በመጠባበቅ ላይ ናው ፍላጎቶን እውን ለማድረግ ፈጥነው ይመዝገቡ ። ✅
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the university
Telephone
Address
Shenkor
Harar
65,ETHIOPIA,